Friday, May 30, 2014

Hadith ቁጥር 4 ‪ልብን ማጥራትና ስራን ማሳመር




Hadith ቁጥር 4

 
ከአቡ ሑረይራ እንደተዘገበው የአላህ መልዕክተኛ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል ‹‹አላህ ወደመልካችሁና ወደ ገንዘቦቻችሁ አይመለከትም ነገር ግን ወደ ልቦቻችሁና ወደ ስራዎቻችሁ ይመለከታል ፡፡ (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል) 

1.ከሰዎች የሚፈለገው ትልቁ ነገር የፀዳ ልብና ያማረ ተግባር ነው፡፡
2.ልብን ማፅዳት ማለት ከሽርክ ፣ ከምቀኝነት ፣ በሰዎች ከመመካት ፣ ሙስሊምን ከመጥላትና ከመሳሰሉት የልብ በሽታዎች መጠበቅ ማለት ሲሆን ነብዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ልብ ካማረ አካል ሙሉ ያምራል ብለዋል፡፡
3.ስራ ተቀባይነት የሚኖረው ለአላህ ብቻ ጥርት ተደርጎ ሲሰራና የነብዩን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) መመሪያ የተከተለ ሲሆን ብቻ ነው፡፡
4.መልካም ስራን ማብዛት አላህ ዘንድ ደረጃን ከፍ ያደርጋል፡፡
5.ሰዎች የሚለኩት በውበትና በገንዘብ ሳይሆን ለአላህ ባላቸው ፍራቻና መልካም ስራ ነው፡፡
6.አላህ ሀብት የሰጠው ሰው ሀብቱን በመልካም ነገር ላይ ካላዋለው አላህ ዘንድ ይጠየቅበታል፡፡
7.ሙስሊም ገንዘብ ስሌለለው መናቅ ወይም ገንዘቡ ብሎ ማክበር የሙስሊም ባህሪ አይደለም


የተወሰደ።

No comments:

Post a Comment