Sunday, May 18, 2014

ሰላት


Photo: ‎ትምህርት ቁጥር 36

#ሰላት

ሚያዝያ 13/8/2006 

ግዴታ ስለመሆኑ፡-
ሰላት ግዴታ መሆኑ በቁርአን በሀዲስና በዑለማዎች ስምምነትም (ኢጅማዕ) የተረጋገጠ ነው፡፡ አላህ እንዲህ ብሏል፡-
‹‹ሶላትንም ደንቡን ጠብቃችሁ ስገዱ፡፡›› (አል በቀራህ 43)
በዚህ መልኩ በብዙ አንቀፆች ላይ ተናግሯል፡፡
በሌላም አንቀፅ አላህ እንዲህ ብሏል፡-
‹‹ለእነዚያ ላመኑት ባሮቼ በእርሱ ውስጥ ሽያጭና ወዳጂነት የሌለበት ቀን ከመምጣቱ በፊት ሶላትን በደንቡ ይሰግዳሉ፡፡›› (አል ኢብራሂም 31)

ከሀዲስ ማስረጃዎች ውሰጥም ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል
 “ሰላቶች አምሰት ምንዳቸው ግን ሀምሳ ነው፡፡”(ቡኻሪ ዘግበውታል)
ቡኻሪና ሙሰሊም በዘገቡት ሀዲስ ስለ ኢስላም ለጠየቃቸው ግለሰብ እንዲህ ብለውታል
 “በቀንና በሌሊት ውስጥ አምስት ሰላቶችን መስገድ…” ጠያቅውም ከዚህ ሌላ አለብኝን? ሲላቸው አይ በራስህ ፈቃድ ከሰገድክ እንጂ ሌላ ግዴታ ሰላት የለምብህም ብለውታል፡፡”

ሰላት ግዴታ የሚሆነው አቅመ አዳም በደረሰና አእምሮ ጤናማ በሆነ ሙስሊም ላይ ሲሆን ካፊር ህፃንና እብድ ላይ ግዴታ አይደለም፡፡ ነብዩ እንዲህ ብለዋል
 “ከሶስት ሰዎች ብዕር ተነስቷል (ወንጀል አይፃፍባቸውም ማለት ነው) የተኛ እስኪነቃ፣ እብድ እስኪድንና ህፃን እስኪደርስ፡፡” 

ህፃን ሰባት አመት ሲሞላው ሶላት እንዲሰግድ መታዘዝ ሲኖርበት አስር አመት ሞልቶት ማይሰግድ ከሆነ ደግም በመግረፍ እንዲሰግድ ማድረግ ግዴታ ነው፡፡ የሰላትን ግዴታነት የካደ ወይም የማይሰግድ በዚህ ተግባሩ ከእስልምና ይወጣና ከሀዲ ይሆናል፡፡ 
ነብዩ እንዲህ ብለዋል
 “በእኛና በእነርሱ መካከል ያለው መለያ ሰላት ነው እሱን የተወ በእርግጥ ክዷል፡፡”                 (ሙስሊም ዘግበውታል)
#ሊንኩን_በመጫን_ፔጁን_ላይክ(like) _ያድርጉ =====>
--------------------------------
www.facebook.com/easyfiqh
--------------------------------
ኢንሻ አላህ ጠቃሚ ኢስላማዊ ዕውቀትን ይገበዩበታል!!! 

ሼር ማድረግ እንዳይረሱ‎


ግዴታ ስለመሆኑ፡-
ሰላት ግዴታ መሆኑ በቁርአን በሀዲስና በዑለማዎች ስምምነትም (ኢጅማዕ) የተረጋገጠ ነው፡፡ አላህ እንዲህ ብሏል፡-
‹‹ሶላትንም ደንቡን ጠብቃችሁ ስገዱ፡፡›› (አል በቀራህ 43)
በዚህ መልኩ በብዙ አንቀፆች ላይ ተናግሯል፡፡
በሌላም አንቀፅ አላህ እንዲህ ብሏል፡-
‹‹ለእነዚያ ላመኑት ባሮቼ በእርሱ ውስጥ ሽያጭና ወዳጂነት የሌለበት ቀን ከመምጣቱ በፊት ሶላትን በደንቡ ይሰግዳሉ፡፡›› (አል ኢብራሂም 31)

ከሀዲስ ማስረጃዎች ውሰጥም ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል
“ሰላቶች አምሰት ምንዳቸው ግን ሀምሳ ነው፡፡”(ቡኻሪ ዘግበውታል)
ቡኻሪና ሙሰሊም በዘገቡት ሀዲስ ስለ ኢስላም ለጠየቃቸው ግለሰብ እንዲህ ብለውታል
“በቀንና በሌሊት ውስጥ አምስት ሰላቶችን መስገድ…” ጠያቅውም ከዚህ ሌላ አለብኝን? ሲላቸው አይ በራስህ ፈቃድ ከሰገድክ እንጂ ሌላ ግዴታ ሰላት የለምብህም ብለውታል፡፡”

ሰላት ግዴታ የሚሆነው አቅመ አዳም በደረሰና አእምሮ ጤናማ በሆነ ሙስሊም ላይ ሲሆን ካፊር ህፃንና እብድ ላይ ግዴታ አይደለም፡፡ ነብዩ እንዲህ ብለዋል
“ከሶስት ሰዎች ብዕር ተነስቷል (ወንጀል አይፃፍባቸውም ማለት ነው) የተኛ እስኪነቃ፣ እብድ እስኪድንና ህፃን እስኪደርስ፡፡” 

ህፃን ሰባት አመት ሲሞላው ሶላት እንዲሰግድ መታዘዝ ሲኖርበት አስር አመት ሞልቶት ማይሰግድ ከሆነ ደግም በመግረፍ እንዲሰግድ ማድረግ ግዴታ ነው፡፡ የሰላትን ግዴታነት የካደ ወይም የማይሰግድ በዚህ ተግባሩ ከእስልምና ይወጣና ከሀዲ ይሆናል፡፡ 
ነብዩ እንዲህ ብለዋል
“በእኛና በእነርሱ መካከል ያለው መለያ ሰላት ነው እሱን የተወ በእርግጥ ክዷል፡፡” (ሙስሊም ዘግበውታል)


ከ www.facebook.com/easyfiqh የተወሰደ።

No comments:

Post a Comment