Tuesday, May 27, 2014

ከአርበዒን አን-ነወውያህ ሓዲሶች የምንወስዳቸው ትምህርቶች 2ኛ እና 3ኛ ሓዲስ የሃይማኖት ደረጃዎች።



2ኛ እና 3ኛ  ሓዲስ

የሃይማኖት ደረጃዎች።

ከሁለተኛው እና  ከሶስተኛው ሓዲስ የምንወስዳቸው ትምህርቶች

1.      ሙስሊሞች ጋር መቀላቀልና ለነሱ ደግሞ መልካም ባህርያትን ማሳየት እንዳለብን
2.     ሌሎች ሰዎችን ለማስተማር ብሎ ዓሊምን መጠየቅ እንደሚቻልና ይህንን ያደረገ ደግሞ ልክ እውቀቱን የሚያሰተላልፈው ሰው አጅር ያገኛል።
3.     እስልምና  አምስት ማእዘናት እንዳሉት። ካለነሱ ደግሞ ዲን እንደማይቆም።
4.     ኢማን ስድስት ማእዘናት እንዳሉት።
5.     እስልምናና ኢማን አብረው ሲጠቀሱ የተለያየ ትርጉም እንዳላቸው። ለየብቻቸው ሲጠቀሱ ግን አንደኛው ሌላኛውን አጠቃሎ እንደሚይዝ።
6.     የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ሶስት ደረጃዎች እንዳላቸው። እነሱም
ኢስላም(ሙስሊም)
ኢማን(ሙእሚን)
ኢሕሳን(ሙሕሲን)

7.     የውመል ቂያማ ሰአቷ የተወሰነ እንደሆነ እና እሷንም የሚያቃት አንድ አላህ ብቻ እንደሆነ። ምልክቶችም እንደላት።

No comments:

Post a Comment