Friday, May 16, 2014

ነብዩ (صلى الله عليه وسلم) መታዘዝ!


ነብዩ (صلى الله عليه وسلم) መታዘዝ!

ከአቡ ሁረይራ እንደተዘገበው የአላህ መልዕክተኛ (صلى الله عليه وسلم) እንዲህ ብለዋል
‹‹ ሁሉም ህዝቦቼ ጀነተን ይገባሉ እምቢ ያለሲቀር የአላህ መልዕክተኛ ሆይ ማነው እምቢ የሚል ሲላቸው፡- እሳቸውም አሉ “የታዘዘኝ ጀነት ገባ እኔን ያመፀ ደግሞ በዕርግጥ እምቢ አለ”›› (ቡኻሪ ዘግበውታል)
ሐዲሡን የዘገቡት ሶሓባ አጭር ታሪክ
‪#‎ስማቸው‬:-አብዱራህማን ኢብኑ ሶኽር ይባላል፡፡አቡ ሑረይራ በሚሠኘው የቅፅል መጠሪያቸው ይታወቃሉ::
‪#‎ከታሪካቸው‬ :-በ7ኛው አመተ ሂጅራ ኢስላምን ተቀበሉ ከነብዩ (صلى الله عليه وسلم) የማይለዩ ስለነበሩ እጅግ በጣም ብዙ ሐዲሶችን በቃላቸው በመሸምደድ ለተተኪው ትውልድ ያስተላለፉ ታላቅ ሶሃቢ ለመሆን በቅተዋል ፡፡ ነብዩ የእውቀት ባለቤት እንዲሆኑ ዱዓ ያደርጉላቸው ስለነበር ታላቅን እውቀት የተጎናፀፉ ነበሩ፡፡
‪#‎ዕለተ_ህልፈት‬:-በ57ኛው አመተ ሂጅራ ነበር
1. ነብዩን (صلى الله عليه وسلم) መታዘዝና እሳቸውን መመሪያ መከተል አማራጭ የሌለው ግዳጅ ነው፡፡
2.የነብዩን (صلى الله عليه وسلم) መመሪያ መከተል የጀነት መግቢያ ምክንያት ነው፡፡
3.ነብዩን (صلى الله عليه وسلم) ማመፅ የጀሀነም መግቢያ ምክንያት ነው፡፡
4.ነብዩን (صلى الله عليه وسلم) መውደድ ማለት ለአላህ የምናደርገውን ኢባዳ (አምልኮ) በአጠቃላይ ከሳቸው በተማርነው መሰረት ብቻ ተፈጻሚ ማድረግ ነው፡፡
5.ነቢያችን (صلى الله عليه وسلم) ለዚህ ኡመት በጣም አዛኝ በመሆናቸው ሰዎች ጀነትንና ጀሀነምን የሚያስገባቸው ስራዎችን ከማመላከት አልተቆጠቡም፡፡
ጠቃሚ ኢስላማዊ ዕውቀትን ለማግኘት ይህን ፔጅ ላይክ (like) ያድርጉ:: 

No comments:

Post a Comment