ኢስላማዊ የሂጃብ መስፈርቶች።
. ስስ ሆኖ የሰውነት ከለርን ማሳየት የለበትም::
. ወፍራምም ሆኖ የሰውነትን ቅርፅ የሚያስገምት መሆን የለበትም::
. ያሸበረቀና እይታን የሚስብ መሆን የለበትም::
. ዋጋው በጣም የተወደደ ዝናን ለማትረፍ የሚለበስ መሆን የለበትም::
. ከወንዶች ልብስ ጋር መመሳሰል የለበትም::
. ከኢስላም ሀይማኖት ውጪ ያሉ (የከሀዲዎችን) ልብስ መምሰል የለበትም::
. ሙሉ የሰውነት ክፍልን መሸፈን አለበት::
وَلَا يُبْدِينَ زِينَتَهُنَّ إِلَّا مَا ظَهَرَ مِنْهَا
«ጌጣቸውንም ከእርሱ ግልጽ ከኾነው በስተቀር አይግለጡ፡፡»
እዚህ ጋር ታላቁ የተፍሲር ባለቤት ኢብኑ ከሲር ይህን አስመልክቶ ዓብደላህ ኢብን መስኡድ እንዲህ ማለቱን ተናግሯል።
“ይህ ማለት ልብሳቸውንና የሚያጣፉትን ማለት ነው” በመቀጠልም ኢብኑ ዓባስና ተከታዮቹ ይህንን በፊትና መዳፎች እንደፈሰሩትም አስቀምጣል።
ተፍሲር ኢብኑ ከሲር።
ሸይኽ አብዱራህማን ቢን ናስር አስሰዕዲ አላህ ይዘንላቸውና ይህን አንቀጽ አስመልክተውም ሲተረጉሙ እንዲህ ብለዋል
“ማለትም ግልጹን ልብሱን ማለት ነው ፡፡ይህም በተለምዶ የሚለበሰው ነው ወደ መፈተን የማይጠራ እስከሆነ ድረስ”
ሌላው እዚህ ጋር አላህ (ሱብሃነሁ ወተአላ) ግልጽ ከሆነው በስተቀር አለ እንጂ ግልጽ ካደረግነው በስተቀር አላለም፡:
ከ www.nesiha.com የተወሰደ።
No comments:
Post a Comment