Friday, December 5, 2014

📌 የሰጋጅ መከለያ (ሱትራ)📌




📌 የሰጋጅ መከለያ (ሱትራ)📌

የሶላት መከለያ ሰጋጅ በራሱና ከፊቱ አቋርጦ በሚያልፍ ሰው መካከል
የሚያደርገው መከለያ ነገር ነው፡፡

√ የሰጋጅ መከለያ ሱትራ የተደነገገ ስለመሆኑ

በጉዞ ላይም ሆነ ከጉዞ ውጭ፣በግዴታም ሆነ በሱንና ሶላት፣በመስጊድም ሆነ በሌላ ቦታ የሰጋጅ መከለያን (ሱትራ) ማድረግ የተደነገገ ነው፡፡

📋 ነቢዩ ﷺ :- ‹‹አንዳችሁ በሚሰግድበት ጊዜ ወደ መከለያ (ሱትራ) ይስገድ፤ወደ መከለያውም ቀረብ ይበል፡፡›› ብለዋልና፡፡
(በአቡ ዳዉድ የተዘገበ)

📋 አል ኢማም አህመድ በዘገቡት ሀዲስ ወህብ (ረዐ) ፡- ‹‹ነቢዩ ﷺ ሚና ላይ ሲያሰግዱን አንካሴ ከፊትለፊታቸው ተከሉና ሁለት ረክዓ መርተው አሰገዱን፡፡» ብለዋል።

√ የሰጋጅ መከለያን የሚመለከት ብያኔ

መከለያ (ሱትራ) ማድረግ ለሰጋጅ ዋጅብ ነው፡፡ ነቢዩ ﷺ ኢማምም ሆነ ለብቻው የሚሰግድ ሰው መከለያ ነገር ከፊት ለፊቱ እንዲደርግ አዘው አበረታተዋል፡፡ በመሆኑም አንድ ሙስሊም በሚሰግድበት ጊዜ ከፊትለፊቱ መከለያ ነገር አድርጎ በርሱና በመከለያው መካከል ሰው አቋርጦ እንዳያልፍ መከልከል ይገበዋል፡፡

📋 ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ «ወደ ሱትራ እንጂ አትስገድ፤ ከፊትለፊትህ እንዲያልፍ ለማንም አትፍቀድ፤ እምቢ ካለህ ከሱ ጋር ሸይጣን አለውና ታገለው።»
ኢብኑ ኹዘይማ ዘግበውታል አልባኒም ሰሂህ ብለውታል።

√ የሰጋጅ መከለያ ያዘለው ጥበብ

መከለያ (ሱትራ) ለሰጋጅ የተደነገገው በርካታ ጥበቦችን አካትቶ ሲሆን ከዚህ ውስጥ፡-

1- ትኩረቱንና ተመስጦውን የሚሻማ በመሆኑ በሚሰግድ ፊት ማቋረጥን ለመከልከል፡፡

2- ሰጋጁ ሙሉ ሃሳቡንና ትኩረቱን በሶላቱ ላይ እንዲያደርግና በሌላ ጣልቃ ገብ እንዳይወሰወስ ለማድረግ፡፡

3- በሴት በውሻ ወይም በአህያ አቋርጦ ማለፍ ሶላት እንዳይቋረጥ ጥንቃቄ ለማድረግ፡፡

📋 ከአቡ ዘር (ረዐ) በተላለፈው መሰረት የአላህ መልእክተኛ ﷺ ፡- ‹‹አንዳችሁ ለመስገድ በሚነሳበት ጊዜ፤ የኮርቻ የኋላ መደገፊያ ያህል ነገር ከፊትለፊቱ ካለ መከለያ ይሆነዋል፤ የኮርቻ የኋላ መደገፊያ ያህል ነገር ከፊትለፊቱ ከሌለ ግን ሶላቱን አህያ፣ሴትና ጥቁር ውሻ ያቋርጥበታል፡፡›› አሉ ሲሉኝ፣ አቡ ዘር ሆይ! ጥቁር ዉሻን ከቀይ ወይም ከብጫ ዉሻ ምን ለየው? አልኳቸውና የወንድሜ ልጅ! አንተ አንደጠየከኝ ሁሉ እኔም የአላህ መልእክተኛን ﷺ ጠይቄ ፡-‹‹ጥቁር ዉሻ ሰይጣን ነው፡፡›› አሉ ብለውኛል፡፡ 
(ሙስሊም ዘግበውታል)

√ ሱትራን ከሚመለከቱ ድንጋጌዎች በከፊል

1- መከለያ ማድረግ ለኢማም ወይም ለብቻው ለሚሰግድም ይሆናል፡፡ ተከትሎ ለሚሰግድ ሰው ኢማሙ ለርሱ መከለያው ነው፡፡

📋 ኢብን ዐባስ (ረዐ) ባስተላለፉት መሰረት ፡- ‹‹የአላህ መልእክተኛ ﷺ በሚና ሰዎችን በማሰገድ ላይ እያሉ፣ ያኔ ለአቅመ አዳም የደረስኩ ነበርኩ፤ አንድ እንስት አህያ ላይ የተቀመጠ ሰው አግኝቼ በአንዳንዶቹ የሶላት ሰፎች ፊት ለፊት አቋርጬ አለፍኩና ከአህያዪቱ ወርጄ እንድ ግጥ ለቀቅኳት፤ ከዚያ ወደ ሶላት ሰፉ ገባሁ፤ ማንም ሰውም ድርጊቴን አልተቃወመም፡፡›› ብለዋል፡፡

ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።
ኢማሙ ነወዊ፤ ይህ ሀዲስ የኢማሙ ሱትራ የሰገሰጆች ሱትራ መሆን እንደሚችል ያሳያል ብለዋል።

የኢማሙ ሱትራ የሰገሰጆችም ሱትራ ስለሆነ በመካከል ሰው ማለፉ ሳይሆን የሚከለከለው በኢማሙ ፊት ማለፉ ነው።

ኢብኑ አብድልበር አልኢስቲዝካር በሚለው መፅሀፋቸው ላይ ይህንን ሲያስረዱ፤ የኢማሙ ሱትራ የሰገሰጆችም ሱትራ እንደሆነ ከሚያስረዱት መካከል ሂሻም ኢብንል ጋዚ ከናፍእ ናፍእ ደግሞ ከኢብኑ ኡመር የዘገቡት ሀዲስ ነው።

ኢብኑ ኡመር እንዲህ ብለዋል፤ 
የአላህ መልእክተኛ ዙህርን ወይም አስርን እያሰገዱ ሳለ እንስሳ ከፊታቸው ልታልፍ ስትሞክር ሊመልሷት ሞከሩ፤ ማለፊያውን ሲያጠቡባትም ትኬሻቸው ግድግዳውን እንደነካ አይቻለው። ከዛም ከበስተጀርባቸው አለፈች።»

ይህም ከበስተጀርባ ስላለፈች ነው።

«የኢማሙ ሱትራ የተከታዮች ሱትራ ነው» የሚለውንም ከኢብኑ ኡመር አብዱረዛቅ ዘንድ ተዘግቧል።

2- በሰጋጅ ሰው ፊት አቋርጦ ማለፍ አይፈቀድም፡፡ ያለፈ ሰው ሀጢያተኛ ይሆናል፡፡

📋 ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል ፡- ‹‹በሚሰግድ ሰው ፊት አቋርጦ የሚያልፍ ሰው ምን (ያህል ከባድ ኃጢአት) እንዳለበት ቢያውቅ ኖሮ አቋርጦት ከሚያልፍ አርባ መቆም የተሻለ በሆነለት ነበር፡፡›› አቡ ነድር - ዘጋቢው - አርባ ቀን ወር ወይም ዓመት ይበሉ አላውቅም ብለዋል፡፡
በቡኻሪና ሙስሊም የተዘገበ

አቋርጦ ማለፉ ከመከለያ ወዲያ ወይም ሰጋጁ መከለያ ካላደረገ ከሱጁዱ ቦታ ራቅ ብሎ ከሆነ ግን ይፈቀዳል፡፡

3- ሰጋጁ አቋርጦት የሚያልፈውን ሰው መከልከል አለበት፡፡

📋 አቡ ሰዒድ አልኹድሪ (ረዐ)
ነቢዩﷺ ፡- ‹‹አንዳችሁ ከሰዎች የሚከልለውን ነገር ከፊቱ አድርጎ ከሰገደና ሌላ ሰው ከፊትለፊቱ አቋርጦ ማለፍ ቢፈልግ ይገፍትረው፣እምቢ ካለም ይፋለመው፤ሰይጣን እንጂ ሌላ አይደለምና፡፡›› ሲሉ ሰምቻለሁ ብለዋል፡፡ ይህንንም በቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።

4- ከእውቀት ባለቤት ዑለማእ መካከል ከፊሎቹ፤ «አስቸጋሪ ሁኔታን ማስወገድ» ከሚል አጠቃላይ መርሕ መሰረት በመካው የተከበረ መስጊድ ሰጋጅ ፊት ማቋረጥን ፈቅደዋል፡፡ ይህም በተከበረው መስጊድ ውስጥ ሰጋጅ ፊት አቋርጦ ማለፍን መከልከል በአብዛኛው ከባድ ችግር የሚፈጥር በመሆኑ ነው፡፡

5- ወደ ግድግዳ ወይም ከመስጊድ ምሶሶዎች መካከል ወይም ከመደርደሪያዎች ወደ አንዱ በመጠጋት ወይም እንደ ዱላ ያለ ነገር በማኖር መከለያ ማድረግ ይቻላል፡፡

6- በሰጋጁና በመከለያው መካከል ያለው ርቀት በአንድ ፍየል መተላፊያ በሚበቃ ያህል ይሰላል፡፡

📋 ሰህል እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹በአላህ መልእክተኛ ﷺ መስገጃና በግድግዳው መካከል የፍል መተላለፊያ ያህል ርቀት ነበር፡፡›› 
በቡኻሪና ሙስሊም የተዘገበ

ማሳሰቢያ፦ 
የሴት ሶላትን መቁረጥ ከላይ በሰፈረውና ‹‹ሶላቱን...ያቋርጥበታል›› በሚለው ሐዲስ ውስጥ ሴትን ከአህያና ከጥቁር ዉሻ ጋር የሚያነጻጽር ነገር የለበትም፡፡ 
የሦስቱ በአንድ ዐረፍተ ነገር አገባብ ውስጥ መገኘት፣ የሦስቱ ማለፍ ሶላት እንዲቋረጥ የሚያደርግበት ምክንያት አንድ ዓይነት ነው ማለት አይደለም፡፡
ማለትም ጥቁር ዉሻ ሶላት የሚቆርጥበት ምክንያት በአህያ ወይም በሴት ሁኔታ ሶላቱ ከሚቋረጥበት ምክንያት ጋር አንድ ነው ማለት አይደለም፡፡ ስለዚህም በሐዲሱ ውስጥ እንደ ተጠቀሰው ጥቁር ዉሻ ሰይጣን መሆኑ አህያ ወይም ሴት ሰይጣን ናቸው ማለት አይደለም፡፡ ሦስቱ በአንድ አገባብ ቢቀርቡም የተለያየ ምክንያት አላቸው፡፡ የዉሻው ምክያት ከተቀሩት ሁለቱ ተለይቶ በሐዲሱ የተጠቀሰ መሆኑ የተለያዩ መሆናቸውን እንጂ ተመሳሳይ መሆናቸውን አያመለክትም።

የሴቷ ሶላት መቁረጥ ከሰጋጁ ቀረብ ብላ አጠገቡ ማለፏ የወንዱን ስሜት ሊቀሰቅስና በሶላቱ ላይ ያለውን ተመስጦና ትኩረቱን ሊበታትንበት ይችል ይሆናል፡፡ ስለዚህም ጠቅለል ባለ መልኩ ሲታይ ከሌላው ወንድ ተላላፊ ይበልጥ ሴት ተላላፊ ትኩረቱን ትስባለች፡፡ ለዚህ ነው -ይበልጥ የሚያውቀው አላህ ነው - በሸሪዓው የሶላትን ተመስጦና ኹሹዕ ለመጠበቅ ሲባል የሴት ልጅን በሰጋጅ ፊት ማለፍ ሶላትን ከሚቆርጡት አንዱ ያደረጋት፡፡

🔚 አይሰስቱ...
ቢያንስ ለ3 ሰው ሼር ያድርጉ!

Source: amharicfiqh.com ከማስተካከያና ጭማሪዎች ጋር የቀረበ።

📹 የሰጋጅ መከለያ (ሱትራ) 

ዓላማችን ኢስላማዊ እውቀትን ማዳረስ ነው::


SHARE

Tuesday, November 25, 2014

4ኛ ሓዲስ الحديث الرابع Amharic Arbeen hadith 4





الحديث الرابع

الخوف من سوء الخاتمة

عَنْ أَبِي عَبْدِ الرَّحْمَنِ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ مَسْعُودٍ قَالَ: حَدَّثَنَا رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم -وَهُوَ الصَّادِقُ الْمَصْدُوقُ-: "إنَّ أَحَدَكُمْ يُجْمَعُ خَلْقُهُ فِي بَطْنِ أُمِّهِ أَرْبَعِينَ يَوْمًا نُطْفَةً، ثُمَّ يَكُونُ عَلَقَةً مِثْلَ ذَلِكَ، ثُمَّ يَكُونُ مُضْغَةً مِثْلَ ذَلِكَ، ثُمَّ يُرْسَلُ إلَيْهِ الْمَلَكُ فَيَنْفُخُ فِيهِ الرُّوحَ، وَيُؤْمَرُ بِأَرْبَعِ كَلِمَاتٍ: بِكَتْبِ رِزْقِهِ، وَأَجَلِهِ، وَعَمَلِهِ، وَشَقِيٍّ أَمْ سَعِيدٍ؛ فَوَاَللَّهِ الَّذِي لَا إلَهَ غَيْرُهُ إنَّ أَحَدَكُمْ لَيَعْمَلُ بِعَمَلِ أَهْلِ الْجَنَّةِ حَتَّى مَا يَكُونُ بَيْنَهُ وَبَيْنَهَا إلَّا ذِرَاعٌ فَيَسْبِقُ عَلَيْهِ الْكِتَابُ فَيَعْمَلُ بِعَمَلِ أَهْلِ النَّارِ فَيَدْخُلُهَا. وَإِنَّ أَحَدَكُمْ لَيَعْمَلُ بِعَمَلِ أَهْلِ النَّارِ حَتَّى مَا يَكُونُ بَيْنَهُ وَبَيْنَهَا إلَّا ذِرَاعٌ فَيَسْبِقُ عَلَيْهِ الْكِتَابُ فَيَعْمَلُ بِعَمَلِ أَهْلِ الْجَنَّةِ فَيَدْخُلُهَا".
رَوَاهُ الْبُخَارِيُّ [رقم:3208]، وَمُسْلِمٌ [رقم:2643].


4ኛ ሓዲስ

የሓዲሱ ትርጉም

ከከፋ (መጥፎ) መጨረሻ መፍራት

ዓብደላህ ኢብን መስዑድ እንዲህ አለ። እውነት ተናጋሪ እና እውነት የተነገራቸው የአላህ መልእክተኛ እንዲህ አሉ። “ እያንዳንዳቹህ በእናቱ ሆድ ውስጥ ፍጥረቱ ይሰበሰባል። አርባ ቀን ንፍጥ የሚመስል ፈሳሽ ይሆናል። ከዛም የረጋ ደምን ይመስላል ለተመሳሳይ ግዜ (40 ቀን)። ከዛም የታኘከን ስጋ ይመስላል ለተመሳሳይ ግዜ (40 ቀን)። ከዛም መልእክተኛ ይላክና ሩሕ ይተነፍስበታል። መልእክተኛውም በአራት ነገሮች ላይ ይታዘዛል። ሲሳዩን፣ ፍጻሜውን፣ ስራውን፣ የተከፋ ወይንም ደስተኛ መሆኑን እንዲጽፍ ይታዘዛል። ከሱውጭ ሌላ በእውነት የሚመለክ አምላክ በሌለው ጌታ እምላሎህ ! አንዳቹህ በሱና በጀነት የስንዝር ያክል ርቀት እስከምትቀረው ድረስ የጀነት ሰዎችን ስራ ይሰራና ከዛም መጨረሻ ላይ መጽሃፉ ይቀድመውና የእሳት ሰዎችን ስራ ይሰራና እሳት ይገባል።ደግሞ አንዳቹህ በሱና በእሳት የስንዝር ያክል ርቀት እስከምትቀረው ድረስ የእሳት ሰዎችን ስራ ይሰራና ከዛም መጨረሻ ላይ መጽሃፉ ይቀድመውና የጀነት ሰዎችን ስራ ይሰራና ጀነት ይገባል።

ሓዲሱን ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።

ከአራተኛው ሓዲስ የምንወስዳቸው ትምህርቶች

1. የሰው ልጅ ሆድ ውስጥ እያለ ለሱ የተመደበ መላኢካ እንዳለ።
2. የሰው ልጅ ሁኔታዎች፣ ሲሳዩ፣ ስራው፣ ፍጻሜው፣ ደስተኛ ነው ወይስ የተከፋ የሚለው ሁሉ ገና በናቱ ሆድ ውስጥ እያለ እንደተጻፈ።
3. በዚች ዓለም የሚከሰተው ክስተት ሁሉ በአላህ የተወሰነ እና ሁሉም ደግሞ ለውሑል መሕፉዝ ላይ የተጻፈነ እንደሆነ።
4. የሰው ልጅ እስኪሞት ድረስ አላህን በመፍራት ላይ መሆን እንዳለበት።
5. ከአላህ መከጀልን(መፈለግን) ማቋረጥ እንደሌለብን።
6. ለሰው ብለን አምልኮን ከመስራት መቆጠብ እንዳለብን። ለሰው ብሎ የሚሰራ ስራው መጨረሻ ላይ እንደሚበላሽበት።
7. ከ 4 ወር በፊት የወረደ ሰው እንዳልሆነ እና ከ 4 ወር ቡኋላ የወረደ ግን ልክ እንደ ማንኛውም ሙስሊም ተገንዞ፣ ሶላተል ጀናዛ ተሰግዶበት ሙስሊሞች ቀብር እንደሚቀበር።


Wednesday, October 22, 2014

ድምጽ መቀየር





ሀምሌ 7/12/2006

ድምጽ መቀየር


አላህ (ሱብሃነሁ ወተአላ) ለምእመናን እናቶች እና እንዲሁም ከነርሱ በኃላ ለሚመጡት አማኝ ሴቶች እንዲህ ብሏል፤-
يَا نِسَاءَ النَّبِيِّ لَسْتُنَّ كَأَحَدٍ مِّنَ النِّسَاءِ ۚ إِنِ اتَّقَيْتُنَّ فَلَا تَخْضَعْنَ بِالْقَوْلِ فَيَطْمَعَ الَّذِي فِي قَلْبِهِ مَرَضٌ وَقُلْنَ قَوْلًا مَّعْرُوفًا [٣٣:٣٢]
« የነቢዩ ሴቶች ሆይ! ከሴቶች እንደማናቸው አይደላችሁም፡፡ አላህን ብትፈሩ (ትበልጣላችሁ)፡፡ያ በልቡ ውስጥ በሽታ ያለበት እንዳይከጅል በንግግር አትለስልሱም፡፡ መልካምንም ንግግር ተናገሩ፡፡ (33:32)
ድምጽ በተቃራኒ ጾታዎች መካከል ባለው ግንኙነት ከፍተኛ የሆነ ሳቢና ማግኔታዊ ሀይል አለው አንዱን ወደሌላው ጠልፎ የሚይዝ ልዩ ወጥመድ ነው:: አላህ (ሱብሃነሁ ወተአላ) አማኝ ሴት መልካምና ቁም ነገሮችን እንጂ ድምጽን በማለሳለስና በማቅለስለስ ወንዶችን ከማማለል እንድትታቀብ ከልክሏታል ፡፡ምክንቱም ይህ ሁኔታ በአዳማጯ ልብ ውስጥ በሽታን ይፈጥራልና ነው፡፡አዎ! ዝሙትን ያስናፍቃል። ለእርሱም ያነሳሳል ይገፋፋል። እዚህ ጋር የድምጽን የአቀየር ስልት በሁለት ከፍለን ልናየው እንችላለን ፡፡
1,ንግግሩን መቀየር ፡-ይህም ማለት አንዲት ሴት ተቃራኒ ጾታን በምታናግርበት ሰአት የተለያዩ የማቆላመጫ ቃላቶችን በመጠቀም ማናገር ነው::
ምሳሌ፡-እከልዬ ስሙን ጠርታ ፣ፍቅሬ ፣ህይወቴና ወዘተ... ይህ ሁኔታ በእውነቱ በቀጥታ መርዝ ነስናሽ አውዳሚ ነገር ነው::
2 በንግግር ውስጥ መለሳለስ፡- ይህ ደግሞ አንዲት ሴት ከተቃራኒ ጾታ ጋር መልካምና ቁም ነገር እያወራች ነገር ግን በውስጡ የምትጠቀማቸው የማለስለስ ፣የመጎተትና የመስለምለም ገጽታዎች ናቸው፡:
ለማንኛውም አንዲት አማኝ ከየትኛውም የፊትና ሙከራዎች አላህን (ሱብሃነሁ ወተአላ) ፈርታ እራሷን ልታቅብ ይገባል፡፡ምስጋና ለአላህ ተገባው፡፡ አትናገሪ አላላትም:: ነገር ግን ድምጷን ተገንና ግርዶ አድርጋ ወንዶችን የፈተናዋ ሰለባ እንዳታደርግ በአጽንኦ ከልክሏታል፡፡ በቃ እጥር ምጥን ቀልጠፍ ቆፍጠን ብሎ መልካምና ቁም ነገሮችን መናገር ዛዛታና እሰጣ ገባ አለመፍጠር:: ሌላው ቁም ነገር ደግሞ እስቲ አንቺ ውዲቷ እህቴ አስተውይ! አላህ እኮ ይህን የከለከለውን መጀመሪያ ያወረደው እጹብ ድንቅ የነብዩ (ﷺ) ሚስቶችና የአማኞች እናት በሆኑት እንስቶች ላይ ነው፡፡ታዲያ እኔና አንቺስ በምን መልኩ ነው መሆን የሚገባን??? እራስን መሸንገል አያዛልቅም:: ይልቁንም ያሉ ግድፈቶችንና መጥፎ ዝንባሌዎችን አርሞ ማስተካከል የብልህ ሰዎች መገለጫ ነው::

Tuesday, September 30, 2014

3ኛ ሓዲስ الحديث الثالث Amharic Arbeen hadith 3



لحديث الثالث

الإسلام

عَنْ أَبِي عَبْدِ الرَّحْمَنِ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عُمَرَ بْنِ الْخَطَّابِ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمَا قَالَ: سَمِعْت رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ: " بُنِيَ الْإِسْلَامُ عَلَى خَمْسٍ: شَهَادَةِ أَنْ لَا إلَهَ إلَّا اللَّهُ وَأَنَّ مُحَمَّدًا رَسُولُ اللَّهِ، وَإِقَامِ الصَّلَاةِ، وَإِيتَاءِ الزَّكَاةِ، وَحَجِّ الْبَيْتِ، وَصَوْمِ رَمَضَانَ".
رَوَاهُ الْبُخَارِيُّ [رقم:8]، وَمُسْلِمٌ [رقم:16].


3ኛ ሓዲስ

የሓዲሱ ትርጉም

የእስልምና ሃይማኖት ደረጃዎች።

ዓብደላህ ኢብን ዑመር የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋሎህ አለ። የአላህ መልእክተኛ እንዲህ አሉ። “ እስልምና አምስት ነገሮች ላይ ተገንብቷል ፦ በእውነት የሚመለክ ጌታ አንድ አላህ ብቻ ነው ብሎ እና ሙሓመድም የአላህ መልእክተኛ ናቸው ብሎ መመስከር፣ ሶላትን በወቅቱና ቀጣይነት ባለው መልኩ መስገድ፣ ዘካን ማውጣት፣ ረመዳንን መጾም፣ የአላህ ቤትን ከቻልን መጎብኘት።”
ሓዲሱን ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።

ከሶስተኛው ሓዲስ የምንወስዳቸው ትምህርቶች

1. እስልምና አምስት ማእዘናት እንዳሉት። ካለነሱ ደግሞ ዲን እንደማይቆም።

Wednesday, August 27, 2014

2ኛ ሓዲስ الحديث الثاني Amharic Arbeen hadith 2






الحديث الثاني

"مجىء جبريل ليعلم المسلمين أمر دينهم"

عَنْ عُمَرَ t أَيْضًا قَالَ: " بَيْنَمَا نَحْنُ جُلُوسٌ عِنْدَ رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ذَاتَ يَوْمٍ، إذْ طَلَعَ عَلَيْنَا رَجُلٌ شَدِيدُ بَيَاضِ الثِّيَابِ، شَدِيدُ سَوَادِ الشَّعْرِ، لَا يُرَى عَلَيْهِ أَثَرُ السَّفَرِ، وَلَا يَعْرِفُهُ مِنَّا أَحَدٌ. حَتَّى جَلَسَ إلَى النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم . فَأَسْنَدَ رُكْبَتَيْهِ إلَى رُكْبَتَيْهِ، وَوَضَعَ كَفَّيْهِ عَلَى فَخْذَيْهِ، وَقَالَ: يَا مُحَمَّدُ أَخْبِرْنِي عَنْ الْإِسْلَامِ. فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم الْإِسْلَامُ أَنْ تَشْهَدَ أَنْ لَا إلَهَ إلَّا اللَّهُ وَأَنَّ مُحَمَّدًا رَسُولُ اللَّهِ، وَتُقِيمَ الصَّلَاةَ، وَتُؤْتِيَ الزَّكَاةَ، وَتَصُومَ رَمَضَانَ، وَتَحُجَّ الْبَيْتَ إنْ اسْتَطَعْت إلَيْهِ سَبِيلًا. قَالَ: صَدَقْت . فَعَجِبْنَا لَهُ يَسْأَلُهُ وَيُصَدِّقُهُ! قَالَ: فَأَخْبِرْنِي عَنْ الْإِيمَانِ. قَالَ: أَنْ تُؤْمِنَ بِاَللَّهِ وَمَلَائِكَتِهِ وَكُتُبِهِ وَرُسُلِهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ، وَتُؤْمِنَ بِالْقَدَرِ خَيْرِهِ وَشَرِّهِ. قَالَ: صَدَقْت. قَالَ: فَأَخْبِرْنِي عَنْ الْإِحْسَانِ. قَالَ: أَنْ تَعْبُدَ اللَّهَ كَأَنَّك تَرَاهُ، فَإِنْ لَمْ تَكُنْ تَرَاهُ فَإِنَّهُ يَرَاك. قَالَ: فَأَخْبِرْنِي عَنْ السَّاعَةِ. قَالَ: مَا الْمَسْئُولُ عَنْهَا بِأَعْلَمَ مِنْ السَّائِلِ. قَالَ: فَأَخْبِرْنِي عَنْ أَمَارَاتِهَا؟ قَالَ: أَنْ تَلِدَ الْأَمَةُ رَبَّتَهَا، وَأَنْ تَرَى الْحُفَاةَ الْعُرَاةَ الْعَالَةَ رِعَاءَ الشَّاءِ يَتَطَاوَلُونَ فِي الْبُنْيَانِ. ثُمَّ انْطَلَقَ، فَلَبِثْنَا مَلِيًّا، ثُمَّ قَالَ: يَا عُمَرُ أَتَدْرِي مَنْ السَّائِلُ؟. قَلَتْ: اللَّهُ وَرَسُولُهُ أَعْلَمُ. قَالَ: فَإِنَّهُ جِبْرِيلُ أَتَاكُمْ يُعَلِّمُكُمْ دِينَكُمْ ". رَوَاهُ مُسْلِمٌ [رقم:8] .

2ኛ ሓዲስ

የሓዲሱ ትርጉም

የእስልምና ሃይማኖት ደረጃዎች።

የሙእሚኖች መሪ የሆነው ዑመር ኢብኒ ኸጣብ እንዲህ አለ። “የሆነ ቀን ከአላህ መልእክተኛ [ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም] ጋር ተቀምጠን እያለ፡ በጣም ጥቁር ጸጉር ያለው፥ በጣም ነጭ ልብስ የለበሰ፥ የመንገደኛ ምልክት የማይታይበት፥ ከኛ ውስጥም ማንም የማያውቀው ሰውዬ ብቅ አለና እነብዩ [ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም] ጋር ተቀመጠ። ጉልበቱን ከጉልበታቸው ጋር አገጣጠመ፥ መዳፉንም ታፋው ላይ አስቀመጠ። ከዛም አንተ ሙሓመድ ሆይ! ስለ ኢስላም ንገረኝ አላቸው። የአላህ መልእክተኛ [ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም] እንዲህ አሉ “ ኢስላም ማለት ፦ በእውነት የሚመለክ ጌታ አንድ አላህ ብቻ ነው ብሎ እና ሙሓመድም የአላህ መልእክተኛ ናቸው ብሎ መመስከር፣ ሶላትን በወቅቱና ቀጣይነት ባለው መልኩ መስገድ፣ ዘካን ማውጣት፣ ረመዳንን መጾም፣ የአላህ ቤትን ከቻልን መጎብኘት።” ሰውየውም “እውነት ተናገርክ” አለ። ዑመርም እንዲህ አለ “በሱ ተገረምን! እሳቸውን ይጠይቃል መልሶ እውነት ተናገርክ ይላቸዋል!” ከዛም ሰውየው ቀጠለና ስለ ኢማን ንገረኝ አላቸው። የአላህ መልእክተኛ[ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም] እንዲህ አሉ “ኢማን ማለት ፦ በአላህ ማመን፣ በመላኢኮች ማመን፣ በመጻህፍት ማመን፣ በመልእክተኞች ማመን፣ በመጨረሻው ቀን ማመን፣ በአላህ ውሳኔ ከፋም በጀም ማመን” ሰውየውም “እውነት ተናገርክ” አለ። ከዛም ሰውየው ቀጠለና ስለ ኢሕሳን ንገረኝ አላቸው። የአላህ መልእክተኛ [ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም] እንዲህ አሉ “ኢሕሳን ማለት አላህን እንደምታየው አድርገህ ልታመልከው ነው፥ አንተ ባታየውም እሱ ያየሃል እና።” ከዛም ሰውየው ቀጠለና የየውመል ቅያማ ሰአቷን ንገረኝ አላቸው። የአላህ መልእክተኛ [ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም] እንዲህ አሉ “ ተጠያቂው ከጠያቂው የበለጠ የሚያውቅ አይደለም” ከዛም ሰውየው ቀጠለና የየውመል ቅያማ ምልክቶቿን ንገረኝ አላቸው። የአላህ መልእክተኛ [ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም] እንዲህ አሉ “ ባርያ ጌታዋን ልትወልድ ነው፣ በባዶ እግራቸው የሚሄዱ፥ እርቃናቸውን የነበሩ፥ ድሆች የነበሩ የፍየል ጠባቂዎች ህንጻ ለመስራት ሲሽቀዳደሙ ልታይ ነው።” ከዛ ቡሃላ ሰውየው ሄደና ብዙ ቆየን። የአላህ መልእክተኛ [ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም] እንዲህ አሉ “አንተ ዑመር ሆይ!ጠያቂው ማን እንደሆነ ታውቃለህን?” ዑመርም “አላህና መልእክተኛው ያወቁ ናቸው።” በማለት መለሰ። የአላህ መልእክተኛ [ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም] እንዲህ አሉ “ የመጣው እኮ ጂብሪል ነው፥ ሃይማኖታቹህን ሊያስተምራቹህ መጣቹህ።”


ሓዲሱን ሙስሊም ዘግቦታል።




ከሁለተኛው ሓዲስ የምንወስዳቸው ትምህርቶች

1. ሙስሊሞች ጋር መቀላቀልና ለነሱ ደግሞ መልካም ባህርያትን ማሳየት እንዳለብን

2. ሌሎች ሰዎችን ለማስተማር ብሎ ዓሊምን መጠየቅ እንደሚቻልና ይህንን ያደረገ ደግሞ ልክ እውቀቱን የሚያሰተላልፈው ሰው አጅር ያገኛል።

3. እስልምና አምስት ማእዘናት እንዳሉት። ካለነሱ ደግሞ ዲን እንደማይቆም።

4. ኢማን ስድስት ማእዘናት እንዳሉት።

5. እስልምናና ኢማን አብረው ሲጠቀሱ የተለያየ ትርጉም እንዳላቸው። ለየብቻቸው ሲጠቀሱ ግን አንደኛው ሌላኛውን አጠቃሎ እንደሚይዝ።

6. የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ሶስት ደረጃዎች እንዳላቸው። እነሱም

ኢስላም(ሙስሊም)

ኢማን(ሙእሚን)

ኢሕሳን(ሙሕሲን)


7. የውመል ቂያማ ሰአቷ የተወሰነ እንደሆነ እና እሷንም የሚውያቃት አንድ አላህ ብቻ እንደሆነ። ምልክቶችም እንደላት።

Tuesday, August 19, 2014

‎ጥንብ_ነችና_ተዋት‬ !!!







ዘረኝነት በነብዩ ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም አንደበት “ጥንብ” እንደሆነ ተገልጿል፡፡
ጥንብ ላይ የሚያንዣብበው ጥንብ አንሳ ነው!!!
ሰው ሁን ከጥንብ ራቅ፡፡ በተቅዋም ከፍ በል፡፡ “ከናተ በላጫችሁ ይበልጥ አላህን የሚፈራው ነው” ብሎናል ጌታችን ሱረቱል ሑጁራት ቁጥር፡ 13 ላይ፡፡ ሐበሻው፣ ጥቁሩ፣ ባሪያው ቢላል፤ ከዐረቡ፣ ከቁረይሹ፣ ከነብዩ ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም አጎት አቡ ለሀብ የመጠቀው በተቀዋው እንጂ በምንም አልነበረም፡፡ ሞኝ አትሁን:: ከእምነትህ ዘርህን አታስቀድም፡፡ አታይም እንዴ አላህ አረቡን፣ ቁረይሹን፣ የነብዩን ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም አጎት አቡ ለሀብን ከሀበሻው ጥቁር ባሪያ በታች ሲያደርገው?!!! መቼም አቡ ለሀብን የሚያወግዝ አንድ የቁርኣን ምእራፍ እንደወረደ የምትዘነጋው አይመስለኝም:: ቢላል ግን በኢማኑ ስንቶች የሚቋምጡበትን ማእረግ ነው የታደለው፡፡ የነብዩ ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም ቅርብ ሰው ነበር፡፡ የነብዩ ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም ሙአዚን መሆን ምንኛ መታደል ነው?!!! እርግጠኛ ነኝ ዛሬም ድረስ ቢላል በሙስሊሞች ልቦና ውስጥ ያለው ቦታ ታላቅ እንደሆነ እስክነግርህ አትጠብቀኝም፡፡
የትኛውንም ቋንቋ ስለተናገርክ ከማንም በላይ አይደለህም፡፡ ከየትኛውም ብሄር ስለመጣህም ከማንም በታች አይደለህም፡፡ ከሁሉ በፊት አንተ ለራስህ ትክክለኛ ቦታህን ስጥ፡፡ ሰዎች ስለሰቀሉህ አትሰቀልም፡፡ ሰዎች ስላወረዱህም አትወርድም፡፡ ለሆሳሱ ሁሉ ስላንተ እየመሰለህ አትሳቀቅ፡፡ ለቃላት መጥፎ ትርጉም እየሰጠህ አትሸማቀቅ፡፡ በትንሽ በትልቁ ውስጥህ አይደፍርስ፡፡ ጥቂት ከጠረጠርክ ሸይጣን ብዙ ያመሳስልብሃል፡፡ በዘሩ ሊኮፈስብህም የሚሻ ካለ፣ በማንነትህ ሊንቅህ ከዳዳው በተቅዋ ብለጠው፡፡ እሱ ጥንብ ቢያነሳ አንተም ጥንብ ታነሳለህ እንዴ?! እስቲ ማነው አህያ ጋዙን ለቀቀብኝ ብሎ እግሩን አንስቶ ጋዝ የሚለቅ? ምናልባት የማይረዳኝ ይኖር ይሆን? እንግዲያው እንዲህ ልበል:- እስቲ ማነው አህያ ፈሳብኝ ብሎ …
ሀላፊነት ይሰማህ፡፡ ቂል የዘረኝነት እሳት ሲያቀጣጥል አንተ ጋዝ አታርከፍክፍ፡፡ ቂል ትከተላለህ እንዴ? የአረሕማን ባሪያዎች ማለት ቂሎች በቂልኛ ሲያናግሯቸው በነገር ሲተነኩሷቸው ነገር እንዲበርድ የሚያደርጉ፣ ሠላም እንዲሰፍን የሚጥሩ ናቸው፡፡ ታዲያ አንተ የማን ባሪያ ነህና?! እርግጠኛ ነኝ “የሸይጣን ነኝ” አትለኝም!! የዘረኛ ዘረኝነት ዘረኛ አያድርግህ፡፡ የጥንብ አንሳው ጥንብ ማንሳት ጥንብ እንደማያስነሳህ ሁሉ፡፡ ሞኝ አትሁን! የሱ ዘረኝነት ላንተ ይቅርታ አይሆንም፡፡ እሱን ሸይጣን ቢጋልበው አንተም ጀርባህን ትሰጣለህ እንዴ? ግን የሸይጣን ፈረስ የሆነ ሰው ምንኛ አስቀያሚ ነው?!!! ያ ረቢ አንተ ጠብቀን፡፡ እናም እልሃለሁ ዘረኛው በቆሻሻ ዘረኝነት ውስጥ ሲዋኝ ብታየው ከቻልክ “አላህን ፍራ” በለው፡፡ በጥንብ እየተጨማለቀ እንደሆነም አስረዳው፡፡ ካልሆነልህ እሱ የያዘውን ጥንብ ለመንጠቅ እንዳትሞክር፤ ወይም ጥንብ ላይ እንዳትሻማ፡፡ ዘረኝነትን በዘረኝነት እንዳትመልስ፡፡ ሸይጣን ከፊት ሲስብህ፣ ከኋላም ሲገፋህ ዝም ብለህ አትነዳ፡፡ “አላህን ፍራ” ማለት ካቃተህ አላህን መፍራት ግን አያቅትህ፡፡ ሂሳብ ስራ ፈሪ ሁን!!! አዎ! አንድየውን፣ ሁሉን አዋቂ፣ ሁሉን ተመልካች፣ የፍርዱ ቀን ዳኛ… የሆነውን ጌታ የምትፈራ ሁን፡፡ አስተውል! “ፈሪ” እባላለሁ ብለህ አትጨነቅ፡፡ የፈራሀው አላህን እንጂ ሰው አይደለም! ቀድሞ ነገር አላህን እንደሚፈራ ሰው ጀግና አለና ነው? በጭራሽ!!! ነብዩስ ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም “ጀግና ማለት በንዴት ጊዜ ቁጣውን የሚውጥ ነው” አላሉም እንዴ? ታዲያ ትእዛዛቸውን እናክብራ! ወዳጅ ያምፃል እንዴ?!
የሌላውን ብሄር፣ ቋንቋ፣… ከማንቋሸሽ ራቅ፡፡ በሌላው ብሄር ላይ ከመሳለቅ ከመቀለድ ተጠንቀቅ፡፡ በሌላው ላይ ሲቀለድም አትሳቅ፡፡ ለራስህ የማትወደውን ነገር በሌላው ላይ አታድርግ፡፡ ይሄ ብዙዎቻችን የተለከፍንበት ገዳይ በሽታ ነው አላህ የጠበቀው ሲቀር፡፡ ምናልባት አንተ ስለራሰህ ደንታ ቢስ ሆነህ ሊሆን ይችላል፡፡ ግን ሁሉ እንዳንተ እንዳልሆነ አትርሳ፡፡
አትጠራጠር! ዘረኝነት የጃሂሊያ ስራ የመሀይሞች መታወቂያ እንደሆነ ታማኙ የአላህ መልእተኛ ነግረውሃል፡፡ ልብ በል! በምትናገረው ቋንቋ ከማንም በታች እንዳልሆንክ ሁሉ ከማንም በላይም አይደለህም! ከፍም ዝቅም የሚያደርግህ ስራህ እንጂ ዘርህ አይደለም፡፡ “ስራው ያስቀረውን ዘሩ አያስቀድመውም!!!” አይደል ያሉን ነብያችን ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም? ነብዩ እኮ ልጃቸው እንኳ “የነብይ ልጅ ነኝ” ብላ እንዳትሸወድ ይልቁንም በርትታ ሰርታ እራሷን እንድታተርፍ ነው አደራ ያሏት፡፡ ከፍ ማለት ከፈለግክ በኢስላም ከፍ በል፣ በተውሒድ ከፍ በል፣ በሱና ከፍ በል፡፡ ከዚህ በራቅክ ቁጥር እየወረደክ፣ እየዘቀጥክ፣ ቁልቁል እየተምዘገዝግክ እንደሆነ ነጋሪ እስኪነግርህ አትጠብቅ፡፡
ጥሪየ ማንነትህን እንድትጥል፣ ማንም በመታወቂያህ ሲረማመድ ዝም እንድትል አይደለም፡፡ ይልቁንም ጥሪየ አላህን እንድትፈራ ሚዛንህ እንድትጠብቅ ብቻ ነው፡፡ እናም የራስህን አስጠብቅ፣ ከሌሎች አትድረስ፡፡ ዘርህን ከእምነትህ ያስቀደምክ እለት ግን አትጠራጠር ታመሃል፡፡ እንዲህ እየገዘገዘህ ህመሙ ካልተሰማህማ ጭራሽ ቫይረሱ አናትህ ላይ ወጥቷል ማለት ነው፡፡ ጓደኛህ ይህን ህመምህን እያየ፣ ጥምብ ስታጨማልቅ እየተመለከተህ ዝም ካለህ፤ ወይ እንደ ተናካሽ ውሻ ያገኘኸውን ስለምትነክስ ፈርቶሃል፣ ወይ ደግሞ እሱም እንዳንተው ጥንብ አንሳ ነው ማለት ነው!!!
አደራ ግን እኔ ይሄን ሁሉ ስለቀልቅ ከችግሩ ነፃ ነኝ እያልኩ አይደለም፡፡ እኔ ቀርቶ ስንት ታላላቆች የሚወድቁበት ችግር እኮ ነው፡፡ ቀድሞ ነገር ታላቅ ሰው ማለት ፍፁም የማይሳሳት ነው እንዴ? ከስህተቱ የሚመለስ ነው እንጂ!!! እናም ቫይረሱ ጋር ላለመድረስ ስንሳሳትም ለመመለስ እንጣር፡፡ እንዲህም እንበል፡ “አላሁመ ኣቲ ነፍሲ ተቅዋሃ፣ ወዘኪሃ አንተ ኸይሩ መን ዘካሃ፣ አንተ ወሊየሃ ወመውላሃ!!!” “ጌታዬ ሆይ አንተ ለነፍሴ ተቅዋዋን ስጣት፡፡ አጥራትም፤ አንተ ከሚያጠራት ሁሉ በላጭ ነህና፡፡ አንተ ረዳቷም ተንከባካቢዋም ነህ”
-----------------
አንብበው ሲጨርሱ ‪#‎ሼር‬ ማድረጉን እንዳይረሱ

Tuesday, August 5, 2014

Amharic Arbeen hadith 1; 1ኛ ሓዲስ



بسم الله الرحمن الرحيم

الحديث الأول 
" إنما الأعمال بالنيات "
عَنْ أَمِيرِ الْمُؤْمِنِينَ أَبِي حَفْصٍ عُمَرَ بْنِ الْخَطَّابِ قَالَ: سَمِعْت رَسُولَ اللَّهِ يَقُولُ: " إنَّمَا الْأَعْمَالُ بِالنِّيَّاتِ، وَإِنَّمَا لِكُلِّ امْرِئٍ مَا نَوَى، فَمَنْ كَانَتْ هِجْرَتُهُ إلَى اللَّهِ وَرَسُولِهِ فَهِجْرَتُهُ إلَى اللَّهِ وَرَسُولِهِ، وَمَنْ كَانَتْ هِجْرَتُهُ لِدُنْيَا يُصِيبُهَا أَوْ امْرَأَةٍ يَنْكِحُهَا فَهِجْرَتُهُ إلَى مَا هَاجَرَ إلَيْهِ". 
رَوَاهُ إِمَامَا الْمُحَدِّثِينَ أَبُو عَبْدِ اللهِ مُحَمَّدُ بنُ إِسْمَاعِيل بن إِبْرَاهِيم بن الْمُغِيرَة بن بَرْدِزبَه الْبُخَارِيُّ الْجُعْفِيُّ [رقم:1]، وَأَبُو الْحُسَيْنِ مُسْلِمٌ بنُ الْحَجَّاج بن مُسْلِم الْقُشَيْرِيُّ النَّيْسَابُورِيُّ 
[رقم:1907] رَضِيَ اللهُ عَنْهُمَا فِي "صَحِيحَيْهِمَا" اللذِينِ هُمَا أَصَحُّ الْكُتُبِ الْمُصَنَّفَةِ.


1ኛ ሓዲስ
የሓዲሱ ትርጉም
ስራዎች ሁሉ የሚመዘኑት በንያ (ባሰብከው ሃሳብ) ነው።
ሁሉም ሰው (የነየተው ነገር) ያሰበው ነገር አለው።
የሙእሚኖች መሪ የሆነው ዑመር ኢብኒ ኸጣብ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋሎህ አለ። የአላህ መልእክተኛ እንዲህ አሉ። “ስራዎች ሁሉ የሚመዘኑት በንያ (ባሰብከው ሃሳብ) ነው። ሁሉም ሰው (የነየተው ነገር) ያሰበው ነገር አለው። ሰው ሁሉ ደግሞ (የነየተውን) ያሰበውን ያገኛል። ስደቱ ወደ አላህ እና ወደ መልእክተኛው ከሆነ፥ ስደቱ ወደ አላህ እና ወደ መልእክተኛው ይሆንለታል። ስደቱ ደግሞ ሊያገኛት ወደሚፈሊጋት አለም (ዱንያ) ወይንም ሊያገባት ወደሚፈልጋት ሴት ከሆነ፥ ስደቱ ወደተሰደተለት ምክንያት ይሆንለታል”
ሓዲሱን ቡኻሪና ሙስሊም ነው የዘገቡት።

ከአንደኛው ሓዲስ የምንወስዳቸው ትምህርቶች

1. ሁሉም ስራ ንያ እንዳለው።
2. ሁሉም ሰው በንያው መሰረት ስራው እንደሚመዘንለት።
3. የሚያስተምር ሰው ምሳሌን እያጠቀሰ ቢያስተምር ጥሩ እንደሆነ።


YOUTUBE.COM|BY ABUADNAN ABUMERIEM


ዝግጅት ፦
በዓብዱልሰመድ መሓመድኑር አሕመድ

Wednesday, July 30, 2014

ሴት ልጅ ካለዎት ታድለዋል!


ሴት ልጅ ካለዎት ታድለዋል! 
በአላህ ስም እጅግ በጣም አዛኝ እና ሩህሩህ በሆነው እጀምራለሁ
የአላህ መልእክተኛ صلى الله عليه وسلم እንዲህ ብለዋል፤
«من ابتلى من هذه البنات بشيء, فأحسن إليهن كن له ستراً من النار» رواه البخاري (5995) ومسلم (2629) وفي لفظ له: (من ابتلى بشيء من البنات فصبر عليهن كن له حجاباً من النار) رواه الترمذي (1913) وصححه الألباني رحمه الله.
(ከእናንተ መካከል ከሴት ልጆቹ ፈተና የገጠመውና፣ ለእነርሱም መልካምን የዋለ ከእሳት ከለላ ይሆኑለታል።)
ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል
ሴት ልጆችን ማሳደግ ከባድ ደረጃ እንዳለው በመግለፅና ልዩ እንክብካቤ እንዲደረግላቸው በማበረታታት
ነው ይህንን ያሉት።
አል አይኒ የተባሉት የሀዲስ ተንታኝ (ኡምደቱል ቃሪ) በተሰኘው ኪታባቸው እንዲህ ብለዋል፤
«እነዚህ ሀዲሶች፤ ከወንድ ልጆች ይልቅ ሴት ልጆች ያላቸውን ሀቅ ያስረግጣሉ፤ ይህም ሴቶች፤ ተሯሩጠው እራሳቸውን ከመቻል አንፃር ደከም ስለሚሉ ነው»
ሴት ልጅሽ የወደፊት እናት ነች።
እናት ደግሞ የልጆች የመጀመሪያ ትምህርት ቤት ነች። ሴት ልጆቻችንን በተለየ ትኩረት ኢስላማዊም ይሁን ዱንያዊ ትምህርቶችን ሸሪአን በጠበቀ መልኩ ማስተማር አለብን።
ሴት ልጅን ማስተማር ማህበረሰብን ማስተማር ነው። በመልካም ሴት ታንፀው የሚያድጉ ልጆች ለወደፊቱ ማህበረሰብ የጀርባ አጥንት ናቸውና ሴቶችን በማስተማር
ሃላፊነት የሚሰማው ትውልድ እንዲፈጠር አስተዋፅኦ እናበርክት።
ሴት ልጅ ከተማረች መብትና ግዴታዋን ስለምታውቅ፤ የባልዋን፣ የወላጆችዋን፣ የልጆችዋን፣ የዘመዶችዋንና፣ የጎረቤቶቿን ሃቅ አላህን በሚያስደስት መልኩ ትጠብቃለች።
የራሷንም መብትና ግዴታ ስለምታውቅ ለበደል አትጋለጥም።
ስለዚህ ለራስዎ፣ለቤተሰብዎ እንዲሁም ለማህበረሰቡ ሲሉ ከጎኗ በመሆን በማረም፣ በማበረታታት፣ በማስተማር እና በመርዳት ሊያግዟት ይገባል።
ውድ ወላጅ!
ልጅዎትን ዲንን በማሳወቅ የተጣለብዎትን ከባድ ሃላፊነት ለመወጣት ከአላህ ከባድ ምንዳ ለማግኘት አሁኑኑ ይንቀሳቀሳሉ ብለን ተስፋ እናደርጋለን።
አላህ ብርታቱን ይስጠዎት!!

#ሊንኩን_በመጫን_ፔጁን_ላይክ(like) _ያድርጉ =====>
--------------------------------
www.facebook.com/tenbihat--------------------------------
ኢንሻ አላህ ጠቃሚ ኢስላማዊ ዕውቀትን ይገበዩበታል!!!
ሼር ማድረግ እንዳይረሱ!

Friday, July 25, 2014

ከረመዳን የመጨረሻዎቹ አስርት ቀናት




ከረመዳን የመጨረሻዎቹ አስርት ቀናት
በጣሀ አህመድ የተዘጋጀ
✔ የረመዳን ወር ታላቅ ወር መሆኑ ለሁላችንም ግልጽ ነው፡፡ ስለታላቅነቱም ብዙ ሳንሰማ ወይም ሳናነብ አልቀረን ይሆናል፡፡ የረመዳን ወር የላቀ ታላቅ ወር እንደመሆኑ ሁሉ ከቀናቶቹና ከለሊቶቹ የመጨረሻዎቹ አስሩ ለየት ያለ ቦታ ሊሰጣቸው የሚገቡ ናቸው፡፡ እነዚህን አሰርት የረመዳን የመጨረሻ ቀናት በተለይም ለሊቶቻቸውን ታላቅ ደረጃ ልንሰጠቸው እንደሚገባ የሚያመለክቱ የተወሰኑ ነጥቦችን በአጭሩ ለመጥቀስ እወዳለሁ፤
✔ አንደኛ፡- የአላህ መልዕክተኛ በነዚህ አስርት ቀናት እና ለሊቶች የነበራቸው የአምልኮ ሁኔታ የምዕመናን እናት ዓኢሻ (ረዲየላዑ ዓንሀ) እንዲህ ብለዋል፡፡ ‹‹የአላህ መልዕክተኛ ከረመዳን የመጨረሻዎቹ አስርት ከሌላ ጊዜ በተለየ መልኩ (በዒባዳ) ላይ ይተጉ ነበር›› ሙስሊም ዘግበውታል
የአላህ መልዕክተኛው የለሊቱ አብዛኛውን ክፍል ከእንቅልፍ በመራቅ ህያው ያደርጉት ነበር፡፡
ዓኢሻ (ረዲየላዑ ዓንሀ) እንዲህ ብለዋል፡፡ ‹‹ የአላህ መልዕክተኛ ከረመዳን የመጨረሻዎቹ አሰርት ቀናት ሲገባ ለሊቱን በዒባዳ ላይ በማሳለፍ ህያው ያደርጉ፣ ቤተሰባቸውን ያነቃቁ (ይቀሰቅሱ) ፣ ቀበቷቸውን በማጥበቅ ይተጉ ነበር፡፡›› ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል
በሐዲሱ ውሰጥ ‹‹ቀበቷቸውን ያጠብቁ ነበር›› በሚል የተጠቀሰውን ቃል በተመለከተ ብዙ የሐዲስ ተንታኞች እንዳሉት ‘‘አሽሙራዊ አገላለፅ ሲሆን ለማለት የተፈለገውም በከፍተኛ ሁኔታ በዒባዳ ከመጠመዳቸው በመነሳት ከሴቶቻቸው ይርቁ ነበር ለማለት ነው’’ ፡፡

✔ ሁለተኛ፡- የእነዚህን አሰርት ቀናት እና ለሊቶች ታላቅነት የሚያሳየን በውስጣቸው ‹‹ለይለተል ቀድር›› የተባለችው ለሊት መኖር ነው፡፡ ይህች ለሊት ከሌሎች የምትለይበት ብዙ መለያዎች ያላት ስትሆን ከነርሱም መካከል፡-
1. ቁርአን የወረደባት ለሊት መሆኗ 
2. ከአንደ ሺህ ወራት የምትበልጥ መሆኗ 3. የተባረከች መሆኗ 
4. ጅብሪል በመልዕክት በብዛት የሚወርዱባት መሆኗ 5. ብዙ ሰዎች በከፍተኛ አምልኮ ውሰጥ የሚገቡ ከመሆኑ አንፃር ከእሳት ነፃ የሚወጡባት ለሊት መሆኗ 
6. በዚህች ለሊት አላህ ምንዳውን እንደሚከፍለው በእርግጠኝነት በማመን እንዲሁም ከይዩልኝ እና መሰል ዱንያዊ ፍላጐቶች ርቆ ሰላትን መስገድ ያበዛ ወንጀሉ የሚታበስ መሆኑ ነው፡፡

✔ ሶስተኛው፡- በእነዚህ አስር ቀናት ኢዕቲካፍ መግባት የመልዕክተኛው ሱና ነው፡፡ ኢዕቲካፍ ማለት እራስን ለአምልኮ ብቻ በመወሰን በመስጂድ መዘውተር ነው፡፡
እናታችን ዓኢሻ እንዲህ ብለዋል፤ ‹‹ነብዩ እስኪሞቱ ድረስ ከረመዳን የመጨረሻዎቹን አስርት ቀናት እራሳቸውን ለአምልኮ ብቻ በመወሰን በመስጂድ ይዘወትሩ ነበር፡፡›› ቡኻሪ እና ሙስሊም ዘግበውተል
⇔ ከዚህ በመቀጠል ከኢዕቲካፍ ጋር ተያያዥነት ያለውን ይህንን ፈትዋ ወይም ጥያቄና መልስ እንመለከታለን፡፡
☞ ጥያቄ፡- የኢዕቲካፍ መስፈርቶች የትኞቹ ናቸው? 
ፆም ከመስፈርቶቹ ይካተታልን? አንድ ሰው በኢዕቲካፍ ላይ እያለ በሽተኛን መጠየቅ፣ በግብዣ ቦታ ላይ መገኘት፣ የቤተሰቦቹን ጉዳይ ማስፈፀም፣ አስክሬን መሸኘት ወይም ወደ ስራው መሄድ ይችላልን?

☞ መልስ፡- ሰላተል ጀመዓ በሚሰገድባቸው መስጂዶች ሁሉ ኢዕቲካፍ ማድረግ የተደነገገ ነው፡፡ ነገር ግን ኢዕቲካፍ የሚያደርገው ሠዉ ሰላተል ጁምዓ ግዴታ ከሚሆንባቸው ሰዎች መካከል ከሆነና ከኢዕቲካፍ ቀናት መካከል የጁምዓ ቀን ካለ ሰላተልጁምዓ በሚሰገድበት መስጅድ ውስጥ ኢዕቲካፍን ማድረጉ የተሻለ (በላጭ) ነው፡፡
ፆም የኢዕቲካፍ መስፈርት አይደለም፡፡ 
በኢዕቲካፍ ላይ ያለ ሰው በዚያ ወቅት በሽተኛን አለመጠየቁ፣ ጥሪ ቢቀርብለት በጥሪ ቦታ ላይ አለመገኘቱ፣ የቤተሰቦቹን ጉዳዬች አለማስፈፀሙ፣ አስክሬን አለመሸኘቱ፣ ከመስጂድ ውጪ ወደ ስራው አለመሄዱ ሱና ነው፡፡ ይህም እናታች ዓኢሻ በትክክለኛ ሰነድ እንዲህ ማለታቸው የተረጋገጠ በመሆኑ ነው፡፡ ‹‹በኢዕቲካፍ ላይ ያለ ሰው በሽተኛን አለመጠየቁ፣ የአስክሬን አሸኛኘት ላይ አለመገኘቱ፣ ግንኙነትን አለመፈፀሙም፣ በስሜት ከተቃራኒ ፆታ ጋር አለመነካካቱ፣ አስገዳጅ ለሆነ ጉዳይ ቢሆን እንጂ ከኢዕቲካፍ አለመውጣቱ ሱና ነው፡፡›› አቡዳውድ እና ዳረቁጥኒ ዘግበውታል

ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴ 
አብዱላህ ቢን ቁዑድ 
አብዱረዛቅ ዓፊፊ 
አብዱል ዓዚዝ ኢብን ባዝ

Friday, July 18, 2014

ዘካ



ዘካ:- የስርወ-ቃሉ ቋንቋዊ ትርጉም፦ "መብዛት"፣ "ማደግ"፣ "መጨመር" እንዲሁም "ማወደስ"ና "(ከጉድፈት) ማጥራት"ን የሚያመለክት ነው። 

የዘካ ሸሪዓዊ መልእክት ደግሞ፦ በየተወሰኑ ጊዜያት ከተወሰኑ የንብረት ዓይነቶች ተቆንጥሮ ለተወሰኑ የሕብረተሰብ ክፍሎች በግዴታነት የሚሰጥ የተገደበ ወጪ ነው። 

የዘካህ ድንጋጌ እንደሌሎቹ መለኮታዊ ህግጋት ሁሉ ከአምልኮ ዘርፍነቱ ባሻገር ድንቅ፣ ብርቅና ፅድቅ ጥበቦችንና ዓላማዎችን ያነገበ ነው። 

ሰዎች ሊረዷቸው ከሚችሏቸው ግለሰባዊና ማሕበራዊ ጥቅሞቹና የመፍትሄነት ገፅታዎቹ መካከል፦ 

1. ለችግረኞች መረጃ መሆኑ፣ 
2. ለድሆች መቋቋሚያ መሆኑ፣ 
3. በእምነት ላይ የተመሠረተ የወዳጅነትና የወንድማማችነት ትስስርን ማጥበቁ፣ 
4. ስብዕናን ከስስትና ከንፉግነት ማፅዳቱ፣ 
5. ድሆች ለሀብታሞች ያላቸውን ምልከታ ከምቀኝነት ማጥራቱ 
6. በድህነት ምክንያት የሚፈጸሙ ወንጀሎችን መገደቡ 
7. ከገንዘብ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ጥቅል ኢስላማዊ ጉዳዮችን 
8. ለማቀላጠፍ ምክንያት መሆኑና፣ 
9. የንብረት በረከት ማስከተሉ ጥቂቶቹ ናቸው። 

በኢልያስ አህመድ ከተዘጋጀው “የዘካ ህግጋት አጭር ማብራርያ” የተወሰደ

Tuesday, July 8, 2014

የረመዷን ወር ተከታታይ ትምህርት



የረመዷን ወር ተከታታይ ትምህርት 

አቡ ሁረይራ (ረድየላሁ ዓንሁ) በዘገቡት ሐዲስ ረሱል (ሰለላሁ ዓለይህ ወሰለም)<<የረመዷን ወር ሲገባ የሰማይ በሮች ይከፈታሉ የጀሀነም በሮች ይዘጋሉ ሸይጧኖችም ይታሰራሉ>> ብለዋል
ቡኻሪ ሙስሊም ዘግበውታል 

Saturday, June 28, 2014

ከአርበዒን አን-ነወውያህ 6ኛ ሓዲስ : ሓላል፣ ሓራም፣ እና ተመሳሳይ ነገሮች

الحديث السادس
"إن الحلال بين وإن الحرام بين"

عَنْ أَبِي عَبْدِ اللَّهِ النُّعْمَانِ بْنِ بَشِيرٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمَا، قَالَ: سَمِعْت رَسُولَ اللَّهِ r يَقُولُ: "إنَّ الْحَلَالَ بَيِّنٌ، وَإِنَّ الْحَرَامَ بَيِّنٌ، وَبَيْنَهُمَا أُمُورٌ مُشْتَبِهَاتٌ لَا يَعْلَمُهُنَّ كَثِيرٌ مِنْ النَّاسِ، فَمَنْ اتَّقَى الشُّبُهَاتِ فَقْد اسْتَبْرَأَ لِدِينِهِ وَعِرْضِهِ، وَمَنْ وَقَعَ فِي الشُّبُهَاتِ وَقَعَ فِي الْحَرَامِ، كَالرَّاعِي يَرْعَى حَوْلَ الْحِمَى يُوشِكُ أَنْ يَرْتَعَ فِيهِ، أَلَا وَإِنَّ لِكُلِّ مَلِكٍ حِمًى، أَلَّا وَإِنَّ حِمَى اللَّهِ مَحَارِمُهُ، أَلَّا وَإِنَّ فِي الْجَسَدِ مُضْغَةً إذَا صَلَحَتْ صَلَحَ الْجَسَدُ كُلُّهُ، وَإذَا فَسَدَتْ فَسَدَ الْجَسَدُ كُلُّهُ، أَلَا وَهِيَ الْقَلْبُ".
رَوَاهُ الْبُخَارِيُّ [رقم:52]، وَمُسْلِمٌ [رقم:1599].  

6ኛ  ሓዲስ
ሓላል፣ ሓራም፣ እና ተመሳሳይ ነገሮች
ከስድስተኛው ሓዲስ የምንወስዳቸው ትምህርቶች
1.      ሓላል ሁሉ ግልጽ እንደሆነ፥ ሓራም ሁሉ ግልጽ እንደሆነ። በመካከላቸው ግን ተመሳሳይ ነገሮች እንዳሉ፥ እነዚህን ተመሳሳይ ነገሮች ደግሞ ጥቂት ሰው ብቻ እንደሚያውቃቸው።
2.     አንድ ነገር ሓላል ነው ወይስ ሓራም ብለን ከተጠራጠርን መራቅ እንዳለብን።
3.     ተመሳሳይ ነገሮች የሚሰራ ወደ ግልጽ ሓራም ለመውደቅ ቅርብ እንደሆነ።
4.     በምሳሌኣዊ አነጋገር ማስረዳት እንደሚቻል።
5.     ነብዩ መሓመድ(ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሱሓቦችን በደንብ እያብራሩ እንዳስተማሩ።
6.     ሰው ጥሩና መጥፎ የሚሆነው ዋናው በልቡ እንደሆነ።
7.     የሰው ልጅ ውጩ መበላሸት ውስጡ የመበላሸቱ አመላካች እንደሆነ።

Thursday, June 26, 2014

‪ለጾም አጋዥ የሆኑ መጽሀፎች‬




ለጾም አጋዥ የሆኑ መጽሀፎች‬ 

ከታች ከተዘረዘሩት ሊንኮች ዳውንሎድ በማድረግ ተጠቃሚ ይሁኑ 
ወይም http://cl.ly/WE8G 
ወይም http://cl.ly/WDR1

‪#‎ 3 ፆመኛ የሆነ ሰው‬ ሊተገብራቸው የሚገቡ ተመራጭ ተግባራት ፓምፕሌት---http://bit.ly/letsomena 
ወይም http://cl.ly/WEAh 


Saturday, June 21, 2014

የረመዳን ስጦታ




--ረመዳንን እንዴት መቀበል ይኖርብናል ?

----->በዑስታዝ ሁሴን ኢሳ እና

---->በኡስታዝ ሡሌይማን አብደላህ 

ዳውንሎድ በማድረግ ያድምጡ ለወዳጅ ዘመድዎም ያስተላልፉ 

Thursday, June 19, 2014

መንዙማ




ታላቁ የተከበረው ወር ረመዳን ደርሷል 

ሽርክ ያነገቡ መንዙማዎች ብቅ ብቅ እያሉ ነው 

ሁላችንም እንጠንቀቅ !!!

Tuesday, June 17, 2014

ከአርበዒን አን-ነወውያህ 5ኛ ሓዲስ በዲን አዲስ ነገር ማምጣት የተከለከለ እንደሆነ።


الحديث الخامس
" من أحدث في أمرنا هذا ما ليس منه فهو رد"

عَنْ أُمِّ الْمُؤْمِنِينَ أُمِّ عَبْدِ اللَّهِ عَائِشَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهَا، قَالَتْ: قَالَ: رَسُولُ اللَّهِ r "مَنْ أَحْدَثَ فِي أَمْرِنَا هَذَا مَا لَيْسَ مِنْهُ فَهُوَ رَدٌّ". رَوَاهُ الْبُخَارِيُّ [رقم:2697]، وَمُسْلِمٌ [رقم:1718].

وَفِي رِوَايَةٍ لِمُسْلِمٍ:"مَنْ عَمِلَ عَمَلًا لَيْسَ عَلَيْهِ أَمْرُنَا فَهُوَ رَدٌّ" .  

5ኛ  ሓዲስ

በዲን አዲስ ነገር ማምጣት የተከለከለ እንደሆነ።

ከአምስተኛው ሓዲስ የምንወስዳቸው ትምህርቶች

1.      በዲን አዲስ ነገር የተሰራ ሁሉ ተቀባይነት እንደሌለው። ሰውየው ጥሩ ንያ ቢኖረውም።
2.     በዲን የታዘዝነውን ስራ ባልታዘዝነው መልኩ መስራት የተከለከለ እንደሆነ።

Saturday, June 14, 2014

ሰላት






ክፍል አንድ 

1. ትርጉሙ፦
ሰላት የዓረብኛ ቋንቋ ትርጉሙ ድዓእ (ልመና) ማለት ሲሆን
ሸሪዓዊ ትርጉሙ ደግሞ፦ በተክቢራ የሚጀመርና በማሰላመት የሚጠናቀቅ ለየት ያሉ ንግግሮችና ተግባሮች ማለት ነው፡፡”
2. ትሩፋቱ፦
ሰላት ከሁለቱ የምስክር ቃሎች ቀጥሎ ከባዱ የኢስላም ማዕዘን ከመሆኑም በላይ የኢስላም ዋናው
መሰረት ነው፡፡ አላህ ነብዩን ወደ ሰማይ በማሳረገ ከሰባቱ ሰማይ በላይ እያሉ ይህን ሰላት መደንገኑ በሙስሊሞች ህይወት ላይ ሰላት ወሳኝ ነገር መሆኑን ይጠቁማል፡፡ ነብዩም አንዳች ነገር ሲገጥማቸው ቶሎ ወደ ሰላት ይሮጡ ነበር፡፡ ስለ ሰላት ትሩፋት የሚገልፁ ሀዲሶች በጣም ብዙ ቢሆኑም የተወሰነውን ብቻ እነሆ፡-
ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል 
“አምስቱ ሰላቶች ከጁምዓ እስከ ጁምዓ ከረመዳን እስከ ረመዳን ታላላቅ ወንጀሎችን ሲቀር በመካከላቸው ያሉትን ኃጢአቶች የሚያብሱ ናቸው::”(ሙስሊም ዘግበውታል)

በሌላም ሀዲስ እንዲህ ብለዋል
“እስቲ ንገሩኝ በደጃፋችሁ ወንዝ ቢኖርና በቀን አምስት ጊዜ በትታጠቡ እድፍ ሊኖርባችሁ ይችላል? ሰሃቦችም “አይኖርም” ሲሉ “ይህ የአምስቱ ሰላቶች ምሳሌ ነው አላህ በእነሱ ሰበብ ኃጠአቶችን ያበሳል” አሉ:: (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)


ከ  www.facebook.com/easyfiqh የተወሰደ።

Thursday, June 12, 2014

የወላጅ ሀቅ



የወላጅ ሀቅ

አዘጋጅ፡- ኡስታዝ ሁሴን ዒሳ

አጭር ማብራሪያ፡- አላሁ ሱብሀነሁ ወተዓላ እራሱና መልእክተኛው ን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ከመታዘዝ ቡኋላ ያዘዘበት ታላቅ ተግባር የወላጆች ሀቅ ነው:: ይህም ሙሐደራ የወላጆችን ሀቅ እንድንገነዘብ የሚረዳ ምርጥ ትምህርት ነው:: 

وَقَضَىٰ رَبُّكَ أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا إِيَّاهُ وَبِالْوَالِدَيْنِ إِحْسَانًا ۚ إِمَّا يَبْلُغَنَّ عِندَكَ الْكِبَرَ أَحَدُهُمَا أَوْ كِلَاهُمَا فَلَا تَقُل لَّهُمَا أُفٍّ وَلَا تَنْهَرْهُمَا وَقُل لَّهُمَا قَوْلًا كَرِيمًا [١٧:٢٣



"ጌታህም (እንዲህ ሲል) አዘዘ፡- እርሱን እንጂ ሌላን አትገዙ፡፡ በወላጆቻችሁም መልካምን ሥሩ፡፡ በአንተ ዘንድ ኾነው አንዳቸው ወይም ሁለታቸው እርጅናን ቢደርሱ ፎህ አትበላቸው፡፡ አትገላምጣቸውም፡፡ ለእነርሱም መልካምን ቃል ተናገራቸው፡፡
" (17:23)

وَاخْفِضْ لَهُمَا جَنَاحَ الذُّلِّ مِنَ الرَّحْمَةِ وَقُل رَّبِّ ارْحَمْهُمَا كَمَا رَبَّيَانِي صَغِيرًا [١٧:٢٤]

"ለሁለቱም ከእዝነትህ የመዋረድን ክንፍ ዝቅ አድርግላቸው፡፡ «ጌታዬ ሆይ! በሕፃንነቴ (በርኅራኄ) እንዳሳደጉኝ እዘንልላቸውም» በል፡፡"(17:24)
ዲን የምግብ ብፌ አይደለም የተመቸነን ይዘን ያልተመቸንን የምንተውበት “አንዱን ጥሎ አንዱን አንጠልጥሎ” እንዳይሆን ነገሩ የወላጆቻችንን ሀቅ ልንጠብቅ ይገባል:: 
ልብ በልልኝ ይህችን አያህ

أَفَتُؤْمِنُونَ بِبَعْضِ الْكِتَابِ وَتَكْفُرُونَ بِبَعْضٍ [٢:٨٥]

"በመጽሐፉ ከፊል ታምናላችሁን? በከፊሉም ትክዳላችሁን?" (2:85)
ያ ራህማን ከወላጆቻችን ሃቅ ጠብቀን ! 
ዳውንሎድ በማድረግ ያድምጡ ለወዳጅ ዘመድዎም ያስተላልፉ። 
ከነዚህ አማራጮች አንዱን በመጫን ዳውንሎድ ያድርጉ፡-