Saturday, June 14, 2014

ሰላት






ክፍል አንድ 

1. ትርጉሙ፦
ሰላት የዓረብኛ ቋንቋ ትርጉሙ ድዓእ (ልመና) ማለት ሲሆን
ሸሪዓዊ ትርጉሙ ደግሞ፦ በተክቢራ የሚጀመርና በማሰላመት የሚጠናቀቅ ለየት ያሉ ንግግሮችና ተግባሮች ማለት ነው፡፡”
2. ትሩፋቱ፦
ሰላት ከሁለቱ የምስክር ቃሎች ቀጥሎ ከባዱ የኢስላም ማዕዘን ከመሆኑም በላይ የኢስላም ዋናው
መሰረት ነው፡፡ አላህ ነብዩን ወደ ሰማይ በማሳረገ ከሰባቱ ሰማይ በላይ እያሉ ይህን ሰላት መደንገኑ በሙስሊሞች ህይወት ላይ ሰላት ወሳኝ ነገር መሆኑን ይጠቁማል፡፡ ነብዩም አንዳች ነገር ሲገጥማቸው ቶሎ ወደ ሰላት ይሮጡ ነበር፡፡ ስለ ሰላት ትሩፋት የሚገልፁ ሀዲሶች በጣም ብዙ ቢሆኑም የተወሰነውን ብቻ እነሆ፡-
ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል 
“አምስቱ ሰላቶች ከጁምዓ እስከ ጁምዓ ከረመዳን እስከ ረመዳን ታላላቅ ወንጀሎችን ሲቀር በመካከላቸው ያሉትን ኃጢአቶች የሚያብሱ ናቸው::”(ሙስሊም ዘግበውታል)

በሌላም ሀዲስ እንዲህ ብለዋል
“እስቲ ንገሩኝ በደጃፋችሁ ወንዝ ቢኖርና በቀን አምስት ጊዜ በትታጠቡ እድፍ ሊኖርባችሁ ይችላል? ሰሃቦችም “አይኖርም” ሲሉ “ይህ የአምስቱ ሰላቶች ምሳሌ ነው አላህ በእነሱ ሰበብ ኃጠአቶችን ያበሳል” አሉ:: (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)


ከ  www.facebook.com/easyfiqh የተወሰደ።

No comments:

Post a Comment