Friday, July 18, 2014

ዘካ



ዘካ:- የስርወ-ቃሉ ቋንቋዊ ትርጉም፦ "መብዛት"፣ "ማደግ"፣ "መጨመር" እንዲሁም "ማወደስ"ና "(ከጉድፈት) ማጥራት"ን የሚያመለክት ነው። 

የዘካ ሸሪዓዊ መልእክት ደግሞ፦ በየተወሰኑ ጊዜያት ከተወሰኑ የንብረት ዓይነቶች ተቆንጥሮ ለተወሰኑ የሕብረተሰብ ክፍሎች በግዴታነት የሚሰጥ የተገደበ ወጪ ነው። 

የዘካህ ድንጋጌ እንደሌሎቹ መለኮታዊ ህግጋት ሁሉ ከአምልኮ ዘርፍነቱ ባሻገር ድንቅ፣ ብርቅና ፅድቅ ጥበቦችንና ዓላማዎችን ያነገበ ነው። 

ሰዎች ሊረዷቸው ከሚችሏቸው ግለሰባዊና ማሕበራዊ ጥቅሞቹና የመፍትሄነት ገፅታዎቹ መካከል፦ 

1. ለችግረኞች መረጃ መሆኑ፣ 
2. ለድሆች መቋቋሚያ መሆኑ፣ 
3. በእምነት ላይ የተመሠረተ የወዳጅነትና የወንድማማችነት ትስስርን ማጥበቁ፣ 
4. ስብዕናን ከስስትና ከንፉግነት ማፅዳቱ፣ 
5. ድሆች ለሀብታሞች ያላቸውን ምልከታ ከምቀኝነት ማጥራቱ 
6. በድህነት ምክንያት የሚፈጸሙ ወንጀሎችን መገደቡ 
7. ከገንዘብ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ጥቅል ኢስላማዊ ጉዳዮችን 
8. ለማቀላጠፍ ምክንያት መሆኑና፣ 
9. የንብረት በረከት ማስከተሉ ጥቂቶቹ ናቸው። 

በኢልያስ አህመድ ከተዘጋጀው “የዘካ ህግጋት አጭር ማብራርያ” የተወሰደ

No comments:

Post a Comment