የወላጅ ሀቅ
አዘጋጅ፡- ኡስታዝ ሁሴን ዒሳ
አጭር ማብራሪያ፡- አላሁ ሱብሀነሁ ወተዓላ እራሱና መልእክተኛው ን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ከመታዘዝ ቡኋላ ያዘዘበት ታላቅ ተግባር የወላጆች ሀቅ ነው:: ይህም ሙሐደራ የወላጆችን ሀቅ እንድንገነዘብ የሚረዳ ምርጥ ትምህርት ነው::
وَقَضَىٰ رَبُّكَ أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا إِيَّاهُ وَبِالْوَالِدَيْنِ إِحْسَانًا ۚ إِمَّا يَبْلُغَنَّ عِندَكَ الْكِبَرَ أَحَدُهُمَا أَوْ كِلَاهُمَا فَلَا تَقُل لَّهُمَا أُفٍّ وَلَا تَنْهَرْهُمَا وَقُل لَّهُمَا قَوْلًا كَرِيمًا [١٧:٢٣
"ጌታህም (እንዲህ ሲል) አዘዘ፡- እርሱን እንጂ ሌላን አትገዙ፡፡ በወላጆቻችሁም መልካምን ሥሩ፡፡ በአንተ ዘንድ ኾነው አንዳቸው ወይም ሁለታቸው እርጅናን ቢደርሱ ፎህ አትበላቸው፡፡ አትገላምጣቸውም፡፡ ለእነርሱም መልካምን ቃል ተናገራቸው፡፡
" (17:23)
وَاخْفِضْ لَهُمَا جَنَاحَ الذُّلِّ مِنَ الرَّحْمَةِ وَقُل رَّبِّ ارْحَمْهُمَا كَمَا رَبَّيَانِي صَغِيرًا [١٧:٢٤]
"ለሁለቱም ከእዝነትህ የመዋረድን ክንፍ ዝቅ አድርግላቸው፡፡ «ጌታዬ ሆይ! በሕፃንነቴ (በርኅራኄ) እንዳሳደጉኝ እዘንልላቸውም» በል፡፡"(17:24)
ዲን የምግብ ብፌ አይደለም የተመቸነን ይዘን ያልተመቸንን የምንተውበት “አንዱን ጥሎ አንዱን አንጠልጥሎ” እንዳይሆን ነገሩ የወላጆቻችንን ሀቅ ልንጠብቅ ይገባል::
ልብ በልልኝ ይህችን አያህ
أَفَتُؤْمِنُونَ بِبَعْضِ الْكِتَابِ وَتَكْفُرُونَ بِبَعْضٍ [٢:٨٥]
"በመጽሐፉ ከፊል ታምናላችሁን? በከፊሉም ትክዳላችሁን?" (2:85)
ያ ራህማን ከወላጆቻችን ሃቅ ጠብቀን !
ዳውንሎድ በማድረግ ያድምጡ ለወዳጅ ዘመድዎም ያስተላልፉ።
ከነዚህ አማራጮች አንዱን በመጫን ዳውንሎድ ያድርጉ፡-
No comments:
Post a Comment