Thursday, June 12, 2014

የወላጅ ሀቅ



የወላጅ ሀቅ

አዘጋጅ፡- ኡስታዝ ሁሴን ዒሳ

አጭር ማብራሪያ፡- አላሁ ሱብሀነሁ ወተዓላ እራሱና መልእክተኛው ን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ከመታዘዝ ቡኋላ ያዘዘበት ታላቅ ተግባር የወላጆች ሀቅ ነው:: ይህም ሙሐደራ የወላጆችን ሀቅ እንድንገነዘብ የሚረዳ ምርጥ ትምህርት ነው:: 

وَقَضَىٰ رَبُّكَ أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا إِيَّاهُ وَبِالْوَالِدَيْنِ إِحْسَانًا ۚ إِمَّا يَبْلُغَنَّ عِندَكَ الْكِبَرَ أَحَدُهُمَا أَوْ كِلَاهُمَا فَلَا تَقُل لَّهُمَا أُفٍّ وَلَا تَنْهَرْهُمَا وَقُل لَّهُمَا قَوْلًا كَرِيمًا [١٧:٢٣



"ጌታህም (እንዲህ ሲል) አዘዘ፡- እርሱን እንጂ ሌላን አትገዙ፡፡ በወላጆቻችሁም መልካምን ሥሩ፡፡ በአንተ ዘንድ ኾነው አንዳቸው ወይም ሁለታቸው እርጅናን ቢደርሱ ፎህ አትበላቸው፡፡ አትገላምጣቸውም፡፡ ለእነርሱም መልካምን ቃል ተናገራቸው፡፡
" (17:23)

وَاخْفِضْ لَهُمَا جَنَاحَ الذُّلِّ مِنَ الرَّحْمَةِ وَقُل رَّبِّ ارْحَمْهُمَا كَمَا رَبَّيَانِي صَغِيرًا [١٧:٢٤]

"ለሁለቱም ከእዝነትህ የመዋረድን ክንፍ ዝቅ አድርግላቸው፡፡ «ጌታዬ ሆይ! በሕፃንነቴ (በርኅራኄ) እንዳሳደጉኝ እዘንልላቸውም» በል፡፡"(17:24)
ዲን የምግብ ብፌ አይደለም የተመቸነን ይዘን ያልተመቸንን የምንተውበት “አንዱን ጥሎ አንዱን አንጠልጥሎ” እንዳይሆን ነገሩ የወላጆቻችንን ሀቅ ልንጠብቅ ይገባል:: 
ልብ በልልኝ ይህችን አያህ

أَفَتُؤْمِنُونَ بِبَعْضِ الْكِتَابِ وَتَكْفُرُونَ بِبَعْضٍ [٢:٨٥]

"በመጽሐፉ ከፊል ታምናላችሁን? በከፊሉም ትክዳላችሁን?" (2:85)
ያ ራህማን ከወላጆቻችን ሃቅ ጠብቀን ! 
ዳውንሎድ በማድረግ ያድምጡ ለወዳጅ ዘመድዎም ያስተላልፉ። 
ከነዚህ አማራጮች አንዱን በመጫን ዳውንሎድ ያድርጉ፡-

No comments:

Post a Comment