Wednesday, July 30, 2014

ሴት ልጅ ካለዎት ታድለዋል!


ሴት ልጅ ካለዎት ታድለዋል! 
በአላህ ስም እጅግ በጣም አዛኝ እና ሩህሩህ በሆነው እጀምራለሁ
የአላህ መልእክተኛ صلى الله عليه وسلم እንዲህ ብለዋል፤
«من ابتلى من هذه البنات بشيء, فأحسن إليهن كن له ستراً من النار» رواه البخاري (5995) ومسلم (2629) وفي لفظ له: (من ابتلى بشيء من البنات فصبر عليهن كن له حجاباً من النار) رواه الترمذي (1913) وصححه الألباني رحمه الله.
(ከእናንተ መካከል ከሴት ልጆቹ ፈተና የገጠመውና፣ ለእነርሱም መልካምን የዋለ ከእሳት ከለላ ይሆኑለታል።)
ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል
ሴት ልጆችን ማሳደግ ከባድ ደረጃ እንዳለው በመግለፅና ልዩ እንክብካቤ እንዲደረግላቸው በማበረታታት
ነው ይህንን ያሉት።
አል አይኒ የተባሉት የሀዲስ ተንታኝ (ኡምደቱል ቃሪ) በተሰኘው ኪታባቸው እንዲህ ብለዋል፤
«እነዚህ ሀዲሶች፤ ከወንድ ልጆች ይልቅ ሴት ልጆች ያላቸውን ሀቅ ያስረግጣሉ፤ ይህም ሴቶች፤ ተሯሩጠው እራሳቸውን ከመቻል አንፃር ደከም ስለሚሉ ነው»
ሴት ልጅሽ የወደፊት እናት ነች።
እናት ደግሞ የልጆች የመጀመሪያ ትምህርት ቤት ነች። ሴት ልጆቻችንን በተለየ ትኩረት ኢስላማዊም ይሁን ዱንያዊ ትምህርቶችን ሸሪአን በጠበቀ መልኩ ማስተማር አለብን።
ሴት ልጅን ማስተማር ማህበረሰብን ማስተማር ነው። በመልካም ሴት ታንፀው የሚያድጉ ልጆች ለወደፊቱ ማህበረሰብ የጀርባ አጥንት ናቸውና ሴቶችን በማስተማር
ሃላፊነት የሚሰማው ትውልድ እንዲፈጠር አስተዋፅኦ እናበርክት።
ሴት ልጅ ከተማረች መብትና ግዴታዋን ስለምታውቅ፤ የባልዋን፣ የወላጆችዋን፣ የልጆችዋን፣ የዘመዶችዋንና፣ የጎረቤቶቿን ሃቅ አላህን በሚያስደስት መልኩ ትጠብቃለች።
የራሷንም መብትና ግዴታ ስለምታውቅ ለበደል አትጋለጥም።
ስለዚህ ለራስዎ፣ለቤተሰብዎ እንዲሁም ለማህበረሰቡ ሲሉ ከጎኗ በመሆን በማረም፣ በማበረታታት፣ በማስተማር እና በመርዳት ሊያግዟት ይገባል።
ውድ ወላጅ!
ልጅዎትን ዲንን በማሳወቅ የተጣለብዎትን ከባድ ሃላፊነት ለመወጣት ከአላህ ከባድ ምንዳ ለማግኘት አሁኑኑ ይንቀሳቀሳሉ ብለን ተስፋ እናደርጋለን።
አላህ ብርታቱን ይስጠዎት!!

#ሊንኩን_በመጫን_ፔጁን_ላይክ(like) _ያድርጉ =====>
--------------------------------
www.facebook.com/tenbihat--------------------------------
ኢንሻ አላህ ጠቃሚ ኢስላማዊ ዕውቀትን ይገበዩበታል!!!
ሼር ማድረግ እንዳይረሱ!

No comments:

Post a Comment