Saturday, June 28, 2014

ከአርበዒን አን-ነወውያህ 6ኛ ሓዲስ : ሓላል፣ ሓራም፣ እና ተመሳሳይ ነገሮች

الحديث السادس
"إن الحلال بين وإن الحرام بين"

عَنْ أَبِي عَبْدِ اللَّهِ النُّعْمَانِ بْنِ بَشِيرٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمَا، قَالَ: سَمِعْت رَسُولَ اللَّهِ r يَقُولُ: "إنَّ الْحَلَالَ بَيِّنٌ، وَإِنَّ الْحَرَامَ بَيِّنٌ، وَبَيْنَهُمَا أُمُورٌ مُشْتَبِهَاتٌ لَا يَعْلَمُهُنَّ كَثِيرٌ مِنْ النَّاسِ، فَمَنْ اتَّقَى الشُّبُهَاتِ فَقْد اسْتَبْرَأَ لِدِينِهِ وَعِرْضِهِ، وَمَنْ وَقَعَ فِي الشُّبُهَاتِ وَقَعَ فِي الْحَرَامِ، كَالرَّاعِي يَرْعَى حَوْلَ الْحِمَى يُوشِكُ أَنْ يَرْتَعَ فِيهِ، أَلَا وَإِنَّ لِكُلِّ مَلِكٍ حِمًى، أَلَّا وَإِنَّ حِمَى اللَّهِ مَحَارِمُهُ، أَلَّا وَإِنَّ فِي الْجَسَدِ مُضْغَةً إذَا صَلَحَتْ صَلَحَ الْجَسَدُ كُلُّهُ، وَإذَا فَسَدَتْ فَسَدَ الْجَسَدُ كُلُّهُ، أَلَا وَهِيَ الْقَلْبُ".
رَوَاهُ الْبُخَارِيُّ [رقم:52]، وَمُسْلِمٌ [رقم:1599].  

6ኛ  ሓዲስ
ሓላል፣ ሓራም፣ እና ተመሳሳይ ነገሮች
ከስድስተኛው ሓዲስ የምንወስዳቸው ትምህርቶች
1.      ሓላል ሁሉ ግልጽ እንደሆነ፥ ሓራም ሁሉ ግልጽ እንደሆነ። በመካከላቸው ግን ተመሳሳይ ነገሮች እንዳሉ፥ እነዚህን ተመሳሳይ ነገሮች ደግሞ ጥቂት ሰው ብቻ እንደሚያውቃቸው።
2.     አንድ ነገር ሓላል ነው ወይስ ሓራም ብለን ከተጠራጠርን መራቅ እንዳለብን።
3.     ተመሳሳይ ነገሮች የሚሰራ ወደ ግልጽ ሓራም ለመውደቅ ቅርብ እንደሆነ።
4.     በምሳሌኣዊ አነጋገር ማስረዳት እንደሚቻል።
5.     ነብዩ መሓመድ(ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሱሓቦችን በደንብ እያብራሩ እንዳስተማሩ።
6.     ሰው ጥሩና መጥፎ የሚሆነው ዋናው በልቡ እንደሆነ።
7.     የሰው ልጅ ውጩ መበላሸት ውስጡ የመበላሸቱ አመላካች እንደሆነ።

Thursday, June 26, 2014

‪ለጾም አጋዥ የሆኑ መጽሀፎች‬




ለጾም አጋዥ የሆኑ መጽሀፎች‬ 

ከታች ከተዘረዘሩት ሊንኮች ዳውንሎድ በማድረግ ተጠቃሚ ይሁኑ 
ወይም http://cl.ly/WE8G 
ወይም http://cl.ly/WDR1

‪#‎ 3 ፆመኛ የሆነ ሰው‬ ሊተገብራቸው የሚገቡ ተመራጭ ተግባራት ፓምፕሌት---http://bit.ly/letsomena 
ወይም http://cl.ly/WEAh 


Saturday, June 21, 2014

የረመዳን ስጦታ




--ረመዳንን እንዴት መቀበል ይኖርብናል ?

----->በዑስታዝ ሁሴን ኢሳ እና

---->በኡስታዝ ሡሌይማን አብደላህ 

ዳውንሎድ በማድረግ ያድምጡ ለወዳጅ ዘመድዎም ያስተላልፉ 

Thursday, June 19, 2014

መንዙማ




ታላቁ የተከበረው ወር ረመዳን ደርሷል 

ሽርክ ያነገቡ መንዙማዎች ብቅ ብቅ እያሉ ነው 

ሁላችንም እንጠንቀቅ !!!

Tuesday, June 17, 2014

ከአርበዒን አን-ነወውያህ 5ኛ ሓዲስ በዲን አዲስ ነገር ማምጣት የተከለከለ እንደሆነ።


الحديث الخامس
" من أحدث في أمرنا هذا ما ليس منه فهو رد"

عَنْ أُمِّ الْمُؤْمِنِينَ أُمِّ عَبْدِ اللَّهِ عَائِشَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهَا، قَالَتْ: قَالَ: رَسُولُ اللَّهِ r "مَنْ أَحْدَثَ فِي أَمْرِنَا هَذَا مَا لَيْسَ مِنْهُ فَهُوَ رَدٌّ". رَوَاهُ الْبُخَارِيُّ [رقم:2697]، وَمُسْلِمٌ [رقم:1718].

وَفِي رِوَايَةٍ لِمُسْلِمٍ:"مَنْ عَمِلَ عَمَلًا لَيْسَ عَلَيْهِ أَمْرُنَا فَهُوَ رَدٌّ" .  

5ኛ  ሓዲስ

በዲን አዲስ ነገር ማምጣት የተከለከለ እንደሆነ።

ከአምስተኛው ሓዲስ የምንወስዳቸው ትምህርቶች

1.      በዲን አዲስ ነገር የተሰራ ሁሉ ተቀባይነት እንደሌለው። ሰውየው ጥሩ ንያ ቢኖረውም።
2.     በዲን የታዘዝነውን ስራ ባልታዘዝነው መልኩ መስራት የተከለከለ እንደሆነ።

Saturday, June 14, 2014

ሰላት






ክፍል አንድ 

1. ትርጉሙ፦
ሰላት የዓረብኛ ቋንቋ ትርጉሙ ድዓእ (ልመና) ማለት ሲሆን
ሸሪዓዊ ትርጉሙ ደግሞ፦ በተክቢራ የሚጀመርና በማሰላመት የሚጠናቀቅ ለየት ያሉ ንግግሮችና ተግባሮች ማለት ነው፡፡”
2. ትሩፋቱ፦
ሰላት ከሁለቱ የምስክር ቃሎች ቀጥሎ ከባዱ የኢስላም ማዕዘን ከመሆኑም በላይ የኢስላም ዋናው
መሰረት ነው፡፡ አላህ ነብዩን ወደ ሰማይ በማሳረገ ከሰባቱ ሰማይ በላይ እያሉ ይህን ሰላት መደንገኑ በሙስሊሞች ህይወት ላይ ሰላት ወሳኝ ነገር መሆኑን ይጠቁማል፡፡ ነብዩም አንዳች ነገር ሲገጥማቸው ቶሎ ወደ ሰላት ይሮጡ ነበር፡፡ ስለ ሰላት ትሩፋት የሚገልፁ ሀዲሶች በጣም ብዙ ቢሆኑም የተወሰነውን ብቻ እነሆ፡-
ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል 
“አምስቱ ሰላቶች ከጁምዓ እስከ ጁምዓ ከረመዳን እስከ ረመዳን ታላላቅ ወንጀሎችን ሲቀር በመካከላቸው ያሉትን ኃጢአቶች የሚያብሱ ናቸው::”(ሙስሊም ዘግበውታል)

በሌላም ሀዲስ እንዲህ ብለዋል
“እስቲ ንገሩኝ በደጃፋችሁ ወንዝ ቢኖርና በቀን አምስት ጊዜ በትታጠቡ እድፍ ሊኖርባችሁ ይችላል? ሰሃቦችም “አይኖርም” ሲሉ “ይህ የአምስቱ ሰላቶች ምሳሌ ነው አላህ በእነሱ ሰበብ ኃጠአቶችን ያበሳል” አሉ:: (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)


ከ  www.facebook.com/easyfiqh የተወሰደ።

Thursday, June 12, 2014

የወላጅ ሀቅ



የወላጅ ሀቅ

አዘጋጅ፡- ኡስታዝ ሁሴን ዒሳ

አጭር ማብራሪያ፡- አላሁ ሱብሀነሁ ወተዓላ እራሱና መልእክተኛው ን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ከመታዘዝ ቡኋላ ያዘዘበት ታላቅ ተግባር የወላጆች ሀቅ ነው:: ይህም ሙሐደራ የወላጆችን ሀቅ እንድንገነዘብ የሚረዳ ምርጥ ትምህርት ነው:: 

وَقَضَىٰ رَبُّكَ أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا إِيَّاهُ وَبِالْوَالِدَيْنِ إِحْسَانًا ۚ إِمَّا يَبْلُغَنَّ عِندَكَ الْكِبَرَ أَحَدُهُمَا أَوْ كِلَاهُمَا فَلَا تَقُل لَّهُمَا أُفٍّ وَلَا تَنْهَرْهُمَا وَقُل لَّهُمَا قَوْلًا كَرِيمًا [١٧:٢٣



"ጌታህም (እንዲህ ሲል) አዘዘ፡- እርሱን እንጂ ሌላን አትገዙ፡፡ በወላጆቻችሁም መልካምን ሥሩ፡፡ በአንተ ዘንድ ኾነው አንዳቸው ወይም ሁለታቸው እርጅናን ቢደርሱ ፎህ አትበላቸው፡፡ አትገላምጣቸውም፡፡ ለእነርሱም መልካምን ቃል ተናገራቸው፡፡
" (17:23)

وَاخْفِضْ لَهُمَا جَنَاحَ الذُّلِّ مِنَ الرَّحْمَةِ وَقُل رَّبِّ ارْحَمْهُمَا كَمَا رَبَّيَانِي صَغِيرًا [١٧:٢٤]

"ለሁለቱም ከእዝነትህ የመዋረድን ክንፍ ዝቅ አድርግላቸው፡፡ «ጌታዬ ሆይ! በሕፃንነቴ (በርኅራኄ) እንዳሳደጉኝ እዘንልላቸውም» በል፡፡"(17:24)
ዲን የምግብ ብፌ አይደለም የተመቸነን ይዘን ያልተመቸንን የምንተውበት “አንዱን ጥሎ አንዱን አንጠልጥሎ” እንዳይሆን ነገሩ የወላጆቻችንን ሀቅ ልንጠብቅ ይገባል:: 
ልብ በልልኝ ይህችን አያህ

أَفَتُؤْمِنُونَ بِبَعْضِ الْكِتَابِ وَتَكْفُرُونَ بِبَعْضٍ [٢:٨٥]

"በመጽሐፉ ከፊል ታምናላችሁን? በከፊሉም ትክዳላችሁን?" (2:85)
ያ ራህማን ከወላጆቻችን ሃቅ ጠብቀን ! 
ዳውንሎድ በማድረግ ያድምጡ ለወዳጅ ዘመድዎም ያስተላልፉ። 
ከነዚህ አማራጮች አንዱን በመጫን ዳውንሎድ ያድርጉ፡-

Tuesday, June 10, 2014

(New App) ዝክረ ረመዳን



(New App) ዝክረ ረመዳን


― ― ― ― ― ― ― ― ―

ምስጋና ለአለማቱ ጌታ ለአላህ የተገባ ነው። የአላህ ሰላምና እዝነት በነብያችን ሙሐመድ ﷺ እንዲሁም ቤተሰቦቻቸውና በባልደረቦቻቸው ሁሉ ላይ ይሁን።

ረመዳንን መፃም ከኢስላም መሰረቶች አንዱ ነው። ማንኛውም ኢባዳ ስኬታማ ያደርገን ዘንድ እውቀትን መሰረት ያደረገ ሊሆን ይገባዋል። 

በቅርቡ የረመዳንን ህግጋት የየዘ አዲስ App እንደምንለቅ ቃል በገባነው መሰረት የአላህ ፍቃድ ሆኖ እነሆ ቀርቦላችኋል። 

«ዝክረ ረመዳን» በሚል ርእስ የተዘጋጀው ይህ የሞባይል አፕሊኬሽን App ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ይታመናል። እጅግ ብዙ ጠቃሚ መረጃዎች ተካተውበታል።

በሚገባ በመጠቀም እና ለሌሎችም በማስተላለፍ ሀላፊነትዎን ይወጡ። 

ይህንን App በማዘጋጀት ሂደት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሁሉ አላህ መልካም ምንዳን እንዲከፍላቸው እንለምነዋለን። 

በአላህ ፈቃድ እና እገዛ በቅርቡ፤ የኦሮምኛ እና የትግርኛ ቋንቋዎችን በማከል update ይኖረናል። 

ሸእባን 7/ 1435

ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር

SHARE

Friday, June 6, 2014

የአዛንና ኢቃም ትርጉሞችና ሸሪዓዊ ድንጋጌዎቻቸው




የአዛንና ኢቃም ትርጉሞችና ሸሪዓዊ ድንጋጌዎቻቸው

ሀ. የአዛንና የኢቃም ትርጉም፦

አዛን ማለት የዓረብኛ ቋንቋ ትርጉሙ ማሳወቅ ማለት ነው፡፡ 
አላህ እንዲህ ብሏል፡-
“ይህ) ከአላህና ከመልክተኛው በታላቁ ሐጅ ቀን የወጣ ወደ ሰዎች የሚደርስ ማስታወቂያ ነው”(9:3)

ሸሪዓዊ ትርጉሙ፦ በተወሰኑ ዚክሮች የሰላት ወቅት መድረሱን ማሳወቅ ማለት ነው፡፡
ኢቃማ ማለት ደግሞ የዓረብኛ ቋንቋ ትርጉሙ የተቀመጠን ማስነሳት ማለት ሲሆን ሸሪዓዊ ትርጉሙ በሚታወቁ ዚክሮች ለሰላት እንዲቆም የሚደረግ ጥሪ ማለት ነው፡፡

ለ. ሸሪዓዊ ድንጋጌያቸው፦
አዛንና ኢቃም ለአምስት ሰላቶች ወንዶች ላይ “فرض كفاية” (በተወሰኑ ሰዎች ላይ ብቻ ግዴታ) የሆነ ሲሆን በቂ ሰው ከፈፀመው ግዴታነቱ ከሁሉም ይነሳል፡፡

ሁለተኛ

ትክክለኛ እንዲሆኑ መሟላት ያለባቸው መስፈርቶች
1. ሙስሊም መሆን፡- ካፊር ቢፈፅማቸው ትክክለኛ አይሆኑም
2. አእምሮ ጤናማ መሆን፡- ልክ እንደሌሎች አምልኮቶች እብድ በስካር ላይ ያለና ህፃን ቢፈፅማቸው ትክክል አይሆኑም፡፡
3. ወንድ መሆን፡- ሴት ድምጿ ፈታኝ በመሆኑ አዛን ማድረግ የለባትም፡፡ እንዲሁም ፍናፍንት ከሆነ ወንድነቱ ስለማይታወቅ አዛንና ኢቃም ማድረግ የለበትም፡፡
4. አዛኑን በሰላት ወቅት ማድረግ፡- ለሱብሂና ለጁምዓ የመጀመሪያዎች አዛን ካልሆነ በቀር የሰላት ወቅት ሳይደርስ አዛን ማድረግ አይፈቀድም፡፡ ኢቃም የሚደረገው ደግሞ ሰላት ውስጥ ለመግባት ሲፈለግ መሆን አለበት፡፡
5. አዛንና ኢቃም ሲደረግ ቅደም ተከተላቸውን የጠበቀ ተከታታይ የሆኑ ቃላቶች መሆን አለባቸው፡፡ የአደራረጉ ሁኔታ አራተኛው ነጥብ ላይ ይገለፃል፡፡ 
6. አዛንና ኢቃም ሸሪዓው በደነገጋቸው ቃላቶችና በዓረብኛ ቋንቋ መደረግ አለባቸው፡፡


አዛን ትክክለኛ እንዲሆኑ መሟላት ካለባቸው መስፈርቶች አንዱን ጥቀሱ?

ከ 
የተወሰደ ።


Tuesday, June 3, 2014

የሰላት ወቅቶች። የመግሪብ ሰላት ወቅት ፣ የሱብሂ ሰላት ወቅት





የመግሪብ ሰላት ወቅት

የመግሪብ ሰላት ወቅት ፀሐይ ከጠለቀበት ሰዓት ጀምሮ ደንገዝ እስከሚል (ፀሀይ መጥለቂያ ጋር የሚኖረው የሰማይ ቅላት እስከሚሰወር) ሲሆን መግሪብንም በመጀመሪያው ወቅት ላይ መስገድ ሱና ነው፡፡ ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል 
“ህዝቦቼ መግሪብን ከዋክብት እስኪጠላለፉ ድረስ ካላዘገዩ በመልካም ላይ ናቸው፡፡” (አህመድ አቡዳውድና ሃኪም ዘግበውታል)
የሐጅ ተግባር ላይ ያለ ሰው ግን የሙዝደሊፋን ሌሊት መግሪብን ወደ ዒሻ አዘግይቶ ከዒሻ ጋር መስገዱ የተወደደ ተግባር ነው፡፡
የዒሻ ሰላት ወቅት

የዒሻ ሰላት ወቅት ደግሞ እስከ እኩለ ለሊት የሚቆይ ሲሆን ዒሻን ግን አስቸጋሪ ካልሆነ አዘግይቶ በመጨረሻው ወቅት መስገድ ይበልጥ የተወደደ ነው፡፡ ከዒሻ በፊት መተኛትና ከዒሻ በኋላ ደግሞ ወሬ ማውራት የተጠላ ነው::
አቡ በርዛህ ባስተላለፉት ሀዲስ 
“ነብዩ ከዒሻ በፊት መተኛትና ከዒሻ በኃላ ማውራት ይጠሉ ነበር::”(ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)

የሱብሂ ሰላት ወቅት

የሱብሂ ሰላት ወቅት ደግሞ ጐህ ከቀደደ ጀምሮ ፀሐይ እስክትወጣ ድረስ ሲሆን የጐህ መቅደድ እንደተረጋገጠ ወዲያው መስገድ የተወደደ ነው፡፡
እነዚህ ለሰላት የተደነገጉ ወቅቶች በመሆናቸው ማንኛውም ሙስሊም የሰላት ወቅቶችን እየተጠባበቀ ሳያዘገይ በተወሰነላቸው ወቅቶች ሊሰግድ ይገባል፡፡ አላህ ሰላትን የሚያዘገዩን ሰዎች እንዲህ በማለት ዝቶባቸዋል፡-
‹‹ወዮላቸው ለሰጋጆች፡፡ ለእነዚያ እነርሱ ከስግደታቸው ዘንጊዎች ለኾኑት፤ (ሰጋጆች)፡፡›› (አል ማዑን 4-5)
በሌላ አንቀፅም እንዲህ ብሏል፦
‹‹ከእነሱም በኋላ ሶላትን ያጓደሉ (የተዉ) ፍላጎቶችንም የተከተሉ መጥፎ ምትኮች ተተኩ! የገሀነምንም ሸለቆ በእርግጥ ያገኛሉ፡፡›› (መርየም 59)
ሰላቶችን በወቅቶቻቸው መስገድ አላህ ዘንድ በጣም ከሚወደዱና ብልጫ ካላቸው ስራዎች የሚመደብ ነው፡፡ ነብዩ (ﷺ) አላህ ዘንድ በጣም የሚወደድን ስራ ሲጠየቁ 
“ሰላቶችን በወቅቶቻቸው መስገድ” በማለት መልሰዋል:: (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)

የዕለቱ ጥያቄ ይሳተፉ
ነብዩ (ﷺ) አላህ ዘንድ በጣም የሚወደድን ስራ ሲጠየቁ የመለሱት ምን በማለት ነው?

ከ www.facebook.com/easyfiqh የተወሰደ።


Sunday, June 1, 2014

ከአርበዒን አን-ነወውያህ 4ኛ ሓዲስ ከከፋ (መጥፎ) መጨረሻ መፍራት


الحديث الرابع

عَنْ أَبِي عَبْدِ الرَّحْمَنِ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ مَسْعُودٍ t قَالَ: حَدَّثَنَا رَسُولُ اللَّهِ r -وَهُوَ الصَّادِقُ الْمَصْدُوقُ-: "إنَّ أَحَدَكُمْ يُجْمَعُ خَلْقُهُ فِي بَطْنِ أُمِّهِ أَرْبَعِينَ يَوْمًا نُطْفَةً، ثُمَّ يَكُونُ عَلَقَةً مِثْلَ ذَلِكَ، ثُمَّ يَكُونُ مُضْغَةً مِثْلَ ذَلِكَ، ثُمَّ يُرْسَلُ إلَيْهِ الْمَلَكُ فَيَنْفُخُ فِيهِ الرُّوحَ، وَيُؤْمَرُ بِأَرْبَعِ كَلِمَاتٍ: بِكَتْبِ رِزْقِهِ، وَأَجَلِهِ، وَعَمَلِهِ، وَشَقِيٍّ أَمْ سَعِيدٍ؛ فَوَاَللَّهِ الَّذِي لَا إلَهَ غَيْرُهُ إنَّ أَحَدَكُمْ لَيَعْمَلُ بِعَمَلِ أَهْلِ الْجَنَّةِ حَتَّى مَا يَكُونُ بَيْنَهُ وَبَيْنَهَا إلَّا ذِرَاعٌ فَيَسْبِقُ عَلَيْهِ الْكِتَابُ فَيَعْمَلُ بِعَمَلِ أَهْلِ النَّارِ فَيَدْخُلُهَا. وَإِنَّ أَحَدَكُمْ لَيَعْمَلُ بِعَمَلِ أَهْلِ النَّارِ حَتَّى مَا يَكُونُ بَيْنَهُ وَبَيْنَهَا إلَّا ذِرَاعٌ فَيَسْبِقُ عَلَيْهِ الْكِتَابُ فَيَعْمَلُ بِعَمَلِ أَهْلِ الْجَنَّةِ فَيَدْخُلُهَا".
رَوَاهُ الْبُخَارِيُّ [رقم:3208]، وَمُسْلِمٌ [رقم:2643].  

4ኛ  ሓዲስ

ከከፋ (መጥፎ) መጨረሻ መፍራት

ከአራተኛው ሓዲስ የምንወስዳቸው ትምህርቶች

1.      የሰው ልጅ ሆድ ውስጥ እያለ ለሱ የተመደበ መላኢካ እንዳለ።
2.     የሰው ልጅ ሁኔታዎች፣ ሲሳዩ፣ ስራው፣ ፍጻሜው፣ ደስተኛ ነው ወይስ የተከፋ የሚለው ሁሉ ገና በናቱ ሆድ ውስጥ እያለ እንደተጻፈ።
3.     በዚች ዓለም የሚከሰተው ክስተት ሁሉ በአላህ የተወሰነ እና ሁሉም ደግሞ ለውሑል መሕፉዝ ላይ የተጻፈነ እንደሆነ።
4.     የሰው ልጅ እስኪሞት ድረስ አላህን በመፍራት ላይ መሆን እንዳለበት።
5.     ከአላህ መከጀልን(መፈለግን) ማቋረጥ እንደሌለብን።
6.     ለሰው ብለን አምልኮን ከመስራት መቆጠብ እንዳለብን። ለሰው ብሎ የሚሰራ ስራው መጨረሻ ላይ እንደሚበላሽበት።
7.     ከ 4 ወር በፊት የወረደ ሰው እንዳልሆነ እና ከ 4 ወር ቡኋላ የወረደ ግን ልክ እንደ ማንኛውም ሙስሊም ተገንዞ፣ ሶላተል ጀናዛ ተሰግዶበት ሙስሊሞች ቀብር እንደሚቀበር።