Saturday, October 24, 2015

8ኛ ሓዲስ : ወደ ተውሒድ ጥሪ ማድረግ፥ ሙስሊም ክብር እንዳለው።





الحديث الثامن
الدعوة للتوحيد وبيان حرمة المسلم
عَنْ ابْنِ عُمَرَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمَا، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلىاللهعليهوسلمقَالَ: "أُمِرْت أَنْ أُقَاتِلَ النَّاسَ حَتَّى يَشْهَدُوا أَنْ لَا إلَهَ إلَّا اللَّهُ وَأَنَّ مُحَمَّدًا رَسُولُ اللَّهِ، وَيُقِيمُوا الصَّلَاةَ، وَيُؤْتُوا الزَّكَاةَ؛ فَإِذَا فَعَلُوا ذَلِكَ عَصَمُوا مِنِّي دِمَاءَهُمْ وَأَمْوَالَهُمْ إلَّا بِحَقِّ الْإِسْلَامِ، وَحِسَابُهُمْ عَلَى اللَّهِ تَعَالَى" .
رَوَاهُ الْبُخَارِيُّ [رقم:25]، وَمُسْلِمٌ [رقم:22].


8ኛ ሓዲስ

የሓዲሱ ትርጉም

ወደ ተውሒድ ጥሪ ማድረግ፥ ሙስሊም ክብር እንዳለው።

ተሚም ኢብን አውስ አድ-ዳርይ በዘገበው ሓዲስ የአላህ መልእክተኛ صلى الله عليه وسلم እንዲህ አሉ። “ሰዎች በእውነት የሚመለክ ጌታ አንድ አላህ ብቻ ነው ሙሓመድን የአላህ መልእክተኛ ነው ብለው እስኪመሰክሩ፥ ሶላትን ቀጥ አርገው እስከሚሰግዱ እና ዘካን እስኪያወጡ ድረስ እንድጋደላቸው ታዝዣሎህ። እነዚህን ነገሮች ካደረጉ ግን ደሞቻቸውን እና ገንዘቦቻቸውን የእስልምና ሓቅ ሲቀር ከእኔ ይጠብቃሉ። ሒሳባቸውም አላህ ዘንድ ነው።”

ሓዲሱን ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።



ከስምንተኛው ሓዲስ የምንወስዳቸው ትምህርቶች

1. ወደ ተውሒድ ጥሪ ማድረግ እንዳለብን።

2. ዘካን አልሰጥም ያለ ጦርነት እንደሚከፈትበት።

3. አንድ ሰው ከላይ እስልምናን ካሳየ ስለውስጡን አያገባንም። ሂሳቡ አላህ ዘንድ ነው።

4. ሰው እንደስራው ይመነዳል።መልካም ከሰራ በመልካም መጥፎ ከሰራ በመጥፎ።

5. ሙስሊም ክብር(ደሙ፣ ንብረቱ፣ ክብሩ) እንዳለው። 

No comments:

Post a Comment