Thursday, February 26, 2015

በሒጃብሽ ላይ ፅናት ይኑርሽ!



www.facebook.com/tenbihat የተወሰደ።

በሒጃብሽ ላይ ፅናት ይኑርሽ!

﴿يَا أَيُّهَا النَّبِيُّ قُل لِّأَزْوَاجِكَ وَبَنَاتِكَ وَنِسَاءِ الْمُؤْمِنِينَ يُدْنِينَ عَلَيْهِنَّ مِن جَلَابِيبِهِنَّ ۚ ذَٰلِكَ أَدْنَىٰ أَن يُعْرَفْنَ فَلَا يُؤْذَيْنَ ۗ وَكَانَ اللَّـهُ غَفُورًا رَّحِيمًا﴾
الأحزاب 59


«አንተ ነቢዩ ሆይ! ለሚስቶቸህ፣ ለሴቶች ልጆችህም፣ ለምእምናን ሚስቶችም ከመከናነቢያዎቻቸው በላያቸው ላይ
እንዲለቁ ንገራቸው፡፡ ይህ (በጨዋነታቸው) እንዲታወቁና 
(በባለጌዎች) እንዳይደፈሩ ለመኾን በጣም የቀረበ ነው፡፡ 
አላህም መሓሪ አዛኝ ነው፡፡» 
አል አህዛብ 59

ጅልባብ ማለት ሰውነትን በሙሉ ከላይ ጀምሮ የሚሸፍን ሰፊ የሆነ የልብስ አይነት ነው። አላህ ነብዩን ለሚስቶቻቸው ለልጆቻቸው እንዲሁም ለምእመናት በሙላ ጅልባቦቻቸውን በላያቸው ላይ በመልቀቅ ፊቶቻቸውንና ደረቶቻቸውን ይሸፍኑ ዘንድ እንዲነግሩ አዟቸዋል።

ሴት ልጅ ፊቷን ባእድ ከሆኑና ሙህርሟ ካልሆኑ ወንዶች የመሸፈን ግዴታ እንዳለባት ከቁርንአንና ከሱና የሆኑ ማስረጃዎች አመላክተዋል። አንዲት ሴት ሰውነቷን ከራሷ ጀምሮ እስከ እግሮቿ ድረስ እንድትሸፍን እንዲሁም በእግሯ ላይ ያደረገችው ጌጥ ድምፅ እንዳያሰማ በእግሯ መሬቱን እንዳትመታ ከታዘዘችና በዚህ መልኩ መሸፈን በሷ ላይ ግድ ከሆነ ፊቷን መሸፈኗ ደግሞ በበለጠ ሁኔታ ግድ እንደሚሆንባት ያስተዋይ አእምሮ ባለቤት አይጠራጠርም።

ይህም የሚሆነው ፊቷን በመክፈቷ ሊከሰት የሚችለው ፊትና ጸጉሯን በመክፈቷ ሊከሰት ከሚችለው ፊትና ወይንም የእግር ጥፍሮቿን በመክፈቷ ሊከሰት ከሚችለው ፊትና እጅግ የከበደ በመሆኑ ነው። የአንድ ሙእሚን ሰው አእምሮ የዚህን ሸሪአዊ ህግ ጥበብና ሚስጥር በሚያስተነትን ጊዜ ሴት ልጅ ጸጉሯን አንገቷን ክንዶቿን ባቷንና እግሮቿን ሸፍና እጆቿንና በውበት የተሞላ ፊቷን ከፍታ ትሄድ ዘንድ መፍቀዱ በፍጹም ከሸሪአዊው ጥበብ ጋር ተቃራኒ መሆኑን ያስተውላል።

በአሁን ዘመን ላይ ያለውን የሰዎችን ፊትን በመሸፈን ላይ ያለውን ቸልተኝነት በአንዳንድ ሙስሊም ሃገሮች ሴት ልጅ ከፊቷ ውጪ ያሉትን እንደ ራስ አንገት ደረትና ክንዶቿን ግልታ በየገበያው ላይ በግድ የለሽነት እንድትሄድ እንዳደረገት ያስተዋለ ሰው ሴት ልጅ ፊቷን እንድትሸፍን ያዘዛትን ሸሪአዊ ጥበብ ቁርጠኛ የሆነ ማወቅን ያውቃል።

አንቺ ሙስሊም ሴት ሆይ! አላህን በመፍራት ያንን ከፊትና የጸዳውንና ዋጅብ የሆነውን ከባለቤትና ሙህሪም ከሚሆኑ ወንዶች በስተቀር መላ ሰውነትን የሚሸፍነውን ሸሪአዊ ሂጃብ ልትለብሺ ይገባል። ሴት ልጅ ፊቷንና አንዳንድ የሰውነት ክፍሎቿን ባእድ ለሆኑ ወንዶች መግለጿን ባስተዋልን ጊዜ ብጣም ብዙ የሆኑ ጥፋቶችም ሰብስቦ ይዞ እናገኛለን።

በዚህ ነገር ውስጥ ጥቅም ሊኖር ይችላል ብንል እንኳን ይህ ጥቅም እጅግ በጣም ትንሽ በመሆኑ ከጥፋቶች ውስጥ ተከልሎ ሊታይ አይችልም።

አንዳንዶች የኒቃብን ሸሪዓዊ ብይን አስመልክቶ፤
"ዋጂብ ነው ወይስ መልበሱ በላጭ የሆነ (አፍደል)? " በሚል ጉንጭ አልፋ ክርክር ሴቶችን በማዋከብ ከኒቃብ ያርቃሉ።

ያንቺ አቋም የሚሆነው፤
☞ ዋጂብ ከሆነ መልበስ ግዴታዬን መወጣት ነው!
☞ ዋጂብ ያልሆነ ትርፍ ስራ ከሆነ ከማንም በላይ ወንጀሌን የሚያስምርና ደረጃዬን ከፍ የሚያደርግ መልካም ስራ ያስፈልገኛል የሚል ይሁን።

አላህ ሆይ!

ትክክለኛውን ኢስላማዊ ሂጃብ በመተግበር ላይ ፅናቱን ለግሰኝ!!

www.facebook.com/tenbihat የተወሰደ።

Sunday, February 8, 2015

የጀናዛ ሰላት አሰጋገድ።



የጀናዛ ሰላት አሰጋገድ

አራት ጊዜ ተክቢራ ይደረጋል፤

☞ ከመጀመሪያ ተክቢራ በመቀጠል አል ፋቲሀ (የመክፈቻው ምዕራፍ) ይነበባል። ከዚህም በተጨማሪ አጠር ያለ የቁርአን ምዕራፍ ወይም አንድ ወይም ሁለት አንቀፅ ቢያነብ ጥሩ ነው። ይህንን በማስመልከት ከአብደላህ ኢብን አባስ የተዘገበ ትክክለኛ ሀዲስ ስላለ ነው።


☞ ከዚያም ለሁለተኛ ጊዜ ተክቢራ ይደረጋል፤
ከተሸሁድ ቀጥሎ እንዳለው በነብዩ ላይ ሰለዋት ያወርዳል። ከዚያም በሶስተኛው ተክቢራ ከተደረገ በኃላ እንዲህ ይላል

(اللهم اغفر لِحينا وميتِنا، وشاهدنا وغائبنا، وصغيرنا وكبيرنا، وذَكَرِنا وأنثانَا، اللهم من أحيَيتَهُ منا فأحيه على الإسلام، ومن توفيته منا فَتَوَفهُ على الإيمان، اللهَم اغفر له، وارحمه، وعافه، واعف عنه، وأكرِم نُزُلَه، وَوَسع مُدخَلَه، واغسله بالماء والثلج وِالبرد، ونقه من الخطايا كما ينقى الثوب الأبيض من الدَنس، وأبدلهُ دارا خيرا من داره، وأهلا خيرا من أهله، وأدخله الجنة، وأعذه من عذاب القبر، وعذاب النار، وافسح له في قبره، ونور له فيه، اللهم لا تَحرمنَا أجره ولا تُضِلنا بعده)

(አላሁመ ኢግፊር ሊሐይና ወመይቲና ወሻሂድና ወጋኢቢና ወሰጊሪና ወከቢሪና ወዘከሪና ወኡንሳና አላሁመ መን አህየይተሁ ሚና ፈአህይሂ አለል ኢስላም ወመን ተወፈይተሁ ሚና ፈተወፈሁ አለል ኢማን አላሁመ ኢግፊር ለሁ ወግሲልሁ ቢልማኢ ወሰልጂ ወልበረዲ ወነቂሂ ሚነል ዙኑቢ ወል ኸጣያ ከማ ዩነቀሰውቡል አብየዲ ሚነደነሲ ወአብዲልሁ ዳረን ኸይረን ሚን ዳሪህ ወአህለን ኸይረን ሚን አህሊህ ወአድኺሉሁል ጀነተ ወአዒዙሁ ሚን ዓዛቢል ቀብሪ ወዓዛቢ ናር ወፍሰህ ለሁ ፊ ቀብሪሂ ወናዊርለሁ ፊህ አላሁመ ላተህሪምና አጅረሁ ወላቱዲለና ባዕደሁ።)

ትርጉሙም: “አላህ ሆይ በህይወት ያሉትንም፣ የሞቱትንም፣ በቅርብ ያለውንም ሩቅ ያለውንም፣ ትልልቆችንም፣ ትንንሾችንም፣ ወንዶችንም ፣ ሴቶችንም ማርልን። አላህ ሆይ ከመካከላችን የምትገለውን በእምነት ላይ እንዲሞት አድርገው። አላህ ሆይ ምህረት አድርግለት፣ እዘንለትም፣ ከእሳት ጠብቀው፣ ይቅርም በለው፣ መስተንግዶውን አሳምርለት፣ መግቢያውንም አስፋለት፣ አጢአቱንም በውሃ፣ በበረዶና በቀዝቃዛ ውሃ እጠብለት፣ ነጭ ልበስ ከቆሻሻ እንደሚፀዳው የእርሱንም ወንጀል አፅዳለት፣ ከቤቱ የተሻለ ቤት ከሚስቱ የተሻለ ሚስት ቀይርለት። ወደ ገነት አስገባው፣ ከቀብር ውስጥ ቅጣትና ከእሳትም ቅጣት ጠብቀው ቀብሩንም አስፋለት፣ አብራለት። አላህ ሆይ ምንዳውን አትንፈገን ከእርሱም በኃላ እጣችንን ጥመት አታድርግብን።”
ማለት ነው።

☞ ከአራተኛው ተክቢራ በኃላ በቀኝ ጐኑ ብቻ “አሰላሙአለይኩም” በማለት ያጠናቅቃል።

ተክቢራ በሚደረግበት ጊዜ እጅን ማንሳት ይወደዳል።
√ ሴት ከሆነች ዱዓው ላይ እንዲህ ይባላል፤
(اللهم اغفر لها . . ) (አላሁመ እግፊርለሃ) 
√ ሁለት ከሆኑ ደግሞ (اللهم اغفر لهما . . . ) (አላሁመ እግፊር ለሁማ) 
√ ከሁለት በላይ ከሆኑ ደግሞ (اللهم اغفر لهم . . ) (አላሁመ እግፊር ለሁም) ይባላል። 
√ ሟቹ ህፃን ከሆነ ለእርሱ ምህረትን በዱዓው ውስጥ ከመለመን ይልቅ እንዲህ ይባላል።

(اللهم اجعله فرطا وذُخْرَا لوالديه، وشفيعاَ مُجَابا، اللهم ثقل به موازينهما، وأعظم به أجورهما، وألحقه بصالح سلف المؤمنين، واجعله في كفالة إبراهيم عليه الصلاة والسلام، وَقِهِ برحمتك عذاب الجحيم)

(አላሁመ ኢጅዓሉሁ ፈረጠን ወዙኽረን ሊዋሊደይሂ ፤ ወሸፊዓን ሙጃበን አሏሁመ ሰቂል ቢሂ መዋዚነሁማ፤ ወአዕዚም ቢሂ ኡጁረሁማ፤ ወአልሂቁሁ ቢሷሊሂ ሰለፊልሙእሚኒን፤ ወጅዓልሁ ፊ ከፋለቲ ኢብራሂመ አለይሂ ወሰላቱ ወሰላም ወቂሂ ቢራህመቲከ አዛበል ጀሂም)

√ ትርጉሙም “አላህ ሆይ በወላጆቹ (በወዲያኛው ህይወት) ቀደሞ ሄዶ የሚያመቻች፣ ለችግር ቀን አለኝታ፣ ተሰሚነት ያለው አማላጅ አድርግላቸው፣ አላህ ሆይ የመልካም ስራቸው ሚዛን ማክበጃና የምንዳቸው ማብዣ አድርገው፣ ከደጋግ ምእመናን ጋርም አስጠጋው ከነብዩ ኢብራሂም u እንክብካቤ ስር አድርገው፣ በችሮታህም ከጀሐነም እሳት ጠብቀው።”

☞ ኢማሙ በሟች ላይ ለመስገድ ሲቆም ወንድ ከሆነ በጭንቅላቱ አቅጣጫ ሴት ከሆነች በሰውነቷ መሀል አቅጣጫ መቆሙ ሱና ይሆናል።

☞ አስክሬኑ ወንድና ሴት ከሆኑ ወንዱ ወደ ኢማሙ በኩል ሴቷ ወደ ቂብላ በኩል ይደረጋሉ ።

ከ www.fb.com/easyfiqh የተወሰደ።