Thursday, June 4, 2015

7ኛ ሓዲስ - ዲን መመካከር ነው።










الحديث السابع

"الدين النصيحة"

عَنْ أَبِي رُقَيَّةَ تَمِيمِ بْنِ أَوْسٍ الدَّارِيِّ t أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم قَالَ: "الدِّينُ النَّصِيحَةُ. قُلْنَا: لِمَنْ؟ قَالَ لِلَّهِ، وَلِكِتَابِهِ، وَلِرَسُولِهِ، وَلِأَئِمَّةِ الْمُسْلِمِينَ وَعَامَّتِهِمْ" .
رَوَاهُ مُسْلِمٌ [رقم: 55].

7  ሓዲስ

የሓዲሱ ትርጉም

ዲን መመካከር ነው።

ተሚም ኢብን አውስ አድ-ዳርይ በዘገበው  ሓዲስ ነብዪ صلى الله عليه وسلم  እንዲህ አሉ። “ዲን መመካከር ነው።” ለማን በማለት ሱሓቦች ጠየቁ። እሳቸውም ለአላህ፣ ለመጽሃፉ፣ ለመልእክተኛው፣ ለሙስሊሙ መሪዎች እና ለአጠቃላይ ሙስሊሙ ነው በማለት መለሱ።
ሓዲሱን ሙስሊም ዘግቦታል።

ከሰባተኛው ሓዲስ የምንወስዳቸው ትምህርቶች
1.     ዲን ሁሉ በምክክር የተገደበ እንደሆነ።
2.     መመካከር ለአላህ፣ ለመለአክተኛው መሓመድ(ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)፣ ለሙስሊም መሪዎች፣ እና ለተራው ሙስሊም እንደሆነ።
3.     በምክክር ላይ እንደገፋፋ።
4.     ማጭበርበር(የመመካከር ተቃራኒ ስለሆነ) የተከለከለ እንደሆነ።