Sunday, March 15, 2015

6ኛ ሓዲስ






الحديث السادس

الحرام والحلال وفضل الإجتناب الشبهات

عَنْ أَبِي عَبْدِ اللَّهِ النُّعْمَانِ بْنِ بَشِيرٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمَا، قَالَ: سَمِعْت رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ: "إنَّ الْحَلَالَ بَيِّنٌ، وَإِنَّ الْحَرَامَ بَيِّنٌ، وَبَيْنَهُمَا أُمُورٌ مُشْتَبِهَاتٌ لَا يَعْلَمُهُنَّ كَثِيرٌ مِنْ النَّاسِ، فَمَنْ اتَّقَى الشُّبُهَاتِ فَقْد اسْتَبْرَأَ لِدِينِهِ وَعِرْضِهِ، وَمَنْ وَقَعَ فِي الشُّبُهَاتِ وَقَعَ فِي الْحَرَامِ، كَالرَّاعِي يَرْعَى حَوْلَ الْحِمَى يُوشِكُ أَنْ يَرْتَعَ فِيهِ، أَلَا وَإِنَّ لِكُلِّ مَلِكٍ حِمًى، أَلَّا وَإِنَّ حِمَى اللَّهِ مَحَارِمُهُ، أَلَّا وَإِنَّ فِي الْجَسَدِ مُضْغَةً إذَا صَلَحَتْ صَلَحَ الْجَسَدُ كُلُّهُ، وَإذَا فَسَدَتْ فَسَدَ الْجَسَدُ كُلُّهُ، أَلَا وَهِيَ الْقَلْبُ".
رَوَاهُ الْبُخَارِيُّ [رقم:52]، وَمُسْلِمٌ [رقم:1599].


6ኛ ሓዲስ

የሓዲሱ ትርጉም

ሓላል፣ ሓራም፣ እና ተመሳሳይ ነገሮች

ኑዕማን ኢብኑ በሺር የአላህ መልእክተኛ صلى الله عليه وسلم እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋሎህ አለ። የአላህ መልእክተኛ صلى الله عليه وسلمእንዲህ አሉ። “ ሓላል(የተፈቀደ) ነገር ሁሉ ግልጽ ነው። ሃራምም(የተከለከለም) ነገር ግልጽ ነው። በመካከላቸው ደግሞ ብዙ ሰው የማያውቃቸው ተመሳሳይ ነገሮች አሉ።ከነዚህ ተመሳሳይ ነገሮች ራሱን የጠበቀ በርግጥም ዲኑንና (ሃይማኖቱንና) ክብሩን ነጻ አውጥቷል። በነዚህ ተመሳሳይ ነገሮች ላይ የወደቀ ሓራም (ክልክል)ላይ በርግጥም ወደቀ። ተመሳሳይ ነገሮች ላይ የሚወድቅ ሰው አምሳያው ልክ እንደ ወሰን ላይ የሚጠብቅ፥ እንስሶቹ ወሰን አልፈው የሰው እርሻን ሊበሉ እንደቀረቡበት እረኛ ነው። በርግጥም ሁሉም ንጉስ ወሰን አለው፥ የአላህ ወሰን ደግሞ እርም ያደረጋቸው ነገሮች ናቸው። በርግጥም ሰውነት ውስጥ ቁራጭ ስጋ አለች። እሷ ካማረች(ከተስተካከለች) ሰውነት ሁሉ ያምራል(ይስተካከላል)፥ እሷ ደግሞ ከተበላሸች ሰውነት ሁሉ ይበላሻል። ያች ቁራጭ ስጋም ልብ ናት።”
ሓዲሱን ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።

ከስድስተኛው ሓዲስ የምንወስዳቸው ትምህርቶች

1. ሓላል ሁሉ ግልጽ እንደሆነ፥ ሓራም ሁሉ ግልጽ እንደሆነ። በመካከላቸው ግን ተመሳሳይ ነገሮች እንዳሉ፥ እነዚህን ተመሳሳይ ነገሮች ደግሞ ጥቂት ሰው ብቻ እንደሚያውቃቸው።
2. አንድ ነገር ሓላል ነው ወይስ ሓራም ብለን ከተጠራጠርን መራቅ እንዳለብን።
3. ተመሳሳይ ነገሮች የሚሰራ ወደ ግልጽ ሓራም ለመውደቅ ቅርብ እንደሆነ።
4. በምሳሌኣዊ አነጋገር ማስረዳት እንደሚቻል።
5. ነብዩ መሓመድ(ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሱሓቦችን በደንብ እያብራሩ እንዳስተማሩ።
6. ሰው ጥሩና መጥፎ የሚሆነው ዋናው በልቡ እንደሆነ።
7. የሰው ልጅ ውጩ መበላሸት ውስጡ የመበላሸቱ አመላካች እንደሆነ።