Wednesday, July 29, 2015

እህቴ ለምን ይሆን ይህን መልበስሽ?



ከ ወንድም Sultan Khedir የተወሰደ።

እህቴ ለምን ይሆን ይህን መልበስሽ?
የምእራባውያንን መንገድ መከተልሽ?
የተወዳጆቹን ምእመናት ልብስ መተውሽ?
እኮ ለምን?
እነርሱ እኮ ለኢስላም ያላቸውን ጥላቻም እያንፀባረቁ ይሆናል፣ይህንን ተገንዝበሻል?
በነፃነት ስም እርቃንሽን እንዳስኬዱሽ፣እንዳስቀሩሽ?
መለስ በይ ወደ ጌታሽ
ሞት እንደሆነ እድሜሽን ሳይጠይቅ፣
ምክኒያት ሳይፈልግ ያንኳኳል በርሽን በድንገት ሊወስድሽ፣
ታዲያ ለምን ይሆን መልበስሽ?
ጌታሽ ፊት ቆመሽ ስትጠየቂ?ስትተሳሰቢ
ጌታሽ ለምን እንደለበሽው ምክኒያቱን ሲጠይቅሽ
በተመለከተሽ ወጣት ዓይን ልክ
እርቃንሽን ባየሽ ሰው መጠን
ያኔ ለምን ለበሽ ? ስትባይ
መልስ የለሽም ከፀፀት በቀር
አስቢበት ዱንያ ምን ብታስደስት አጭር እና ጠፊ ነች።
ተመለሽ ጊዜው ሳያልፍ ፀፀት የማይጠቅምበት ጊዜ
ከመምጣቱ በፊት፣
 

Thursday, June 4, 2015

7ኛ ሓዲስ - ዲን መመካከር ነው።










الحديث السابع

"الدين النصيحة"

عَنْ أَبِي رُقَيَّةَ تَمِيمِ بْنِ أَوْسٍ الدَّارِيِّ t أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم قَالَ: "الدِّينُ النَّصِيحَةُ. قُلْنَا: لِمَنْ؟ قَالَ لِلَّهِ، وَلِكِتَابِهِ، وَلِرَسُولِهِ، وَلِأَئِمَّةِ الْمُسْلِمِينَ وَعَامَّتِهِمْ" .
رَوَاهُ مُسْلِمٌ [رقم: 55].

7  ሓዲስ

የሓዲሱ ትርጉም

ዲን መመካከር ነው።

ተሚም ኢብን አውስ አድ-ዳርይ በዘገበው  ሓዲስ ነብዪ صلى الله عليه وسلم  እንዲህ አሉ። “ዲን መመካከር ነው።” ለማን በማለት ሱሓቦች ጠየቁ። እሳቸውም ለአላህ፣ ለመጽሃፉ፣ ለመልእክተኛው፣ ለሙስሊሙ መሪዎች እና ለአጠቃላይ ሙስሊሙ ነው በማለት መለሱ።
ሓዲሱን ሙስሊም ዘግቦታል።

ከሰባተኛው ሓዲስ የምንወስዳቸው ትምህርቶች
1.     ዲን ሁሉ በምክክር የተገደበ እንደሆነ።
2.     መመካከር ለአላህ፣ ለመለአክተኛው መሓመድ(ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)፣ ለሙስሊም መሪዎች፣ እና ለተራው ሙስሊም እንደሆነ።
3.     በምክክር ላይ እንደገፋፋ።
4.     ማጭበርበር(የመመካከር ተቃራኒ ስለሆነ) የተከለከለ እንደሆነ።



Saturday, May 9, 2015

~`~ትዳርህን ተንከባከበው~`~



~`~ትዳርህን ተንከባከበው~`~

የአጋርህን ስሜት ተረድተህ
ሃላፊነትህን ተወጣ
°°°°°°° ✅ °°°°°°°


የተንቢሃት ልዩ ሳምንታዊ መልዕክት ቁ• 11

① ስሜትን መረዳት

ትዳር በህይወታችን ውስጥ ከፍተኛውን ሚና የሚጫወት ሲሆን የግለሰብ፣ የቤተሰብና የማህበረሰብ ኣልፎም ያጠቃላይ የሰው ልጆች መገንቢያ ማዕከል ነው።

በትዳር ዓለም በሌሎች የህይወት ዘርፎች የማይገኙ ክቡር ትሩፋቶች ይገኙበታል።

√ እውነተኛ አፍቃሪ
√ ሚስጥረኛ ወዳጅ
√ ከማንም የቀረበ ነውርን ሸፋኝ
√ የተባረከ ተተኪ ትውልድ
√ ቤተሰብ፣ አዳዲስ ዘመዶች…
√ ሀላል የሆነ እርካታ
√ የኔ ሚባል ደጋፊ እና የመሳሰሉት

ይህ እጅግ በጣም ብዙ ጥቅሞች ያሉበት ትዳር የሚባለውን ፕሮጀክት በአግባቡ ለመምራትና የሚጠበቀውን ጥቅም ለማግኘት ወሳኝ ከሚባሉት ነጥቦች ኣንዱ የትዳር ጓዶቹ መግባባት ነው።

መግባባት ደግሞ የሚወለደው ኣንዱ ያንዱን ስሜትና ፍላጐት ሲገነዘብና አስፈላጊውን ምላሽ ሲሰጥ ነው።

ለዚህም ማስተዋያ እንዲሆነን የአርዓያችንን የህይወት ታሪክ ስናስተውል ከምእመናን እናት ዓኢሻ ቢንቱ ሲዲቅ ረዲየላሁ ዐንሁም ጋር ሳሉ የገጠማቸውን ሲነግሩን እንዲህ ይላሉ።

ሙስሊም በዘገቡት ትክክለኛ ሀዲስ ዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ በሆነ ጉዳይ ቅር ሲላት ወይም ደስተኛ ስትሆን ያውቁባት ነበር።

በዚህም ጥናታቸው ባለቤታቸው በመሃላዋ ውስጥ እንኳን ቅሬታዋን የምትገልፅበትን መንገድ በተከታዩ መልክ ገልፀዋል።

« በኔ ላይ ደስተኛ ስትሆኚም ሆነ በኔ ላይ ስትቆጪ አውቃለሁኝ።

በኔ ላይ ደስተኛ በሆንሽ ግዜ 
በሙሐመድ ጌታ ይሁንብኝ " ትያለሽ።

በኔ ላይ በተቆጣሽ ግዜ ደግሞ:
በኢብራሂም ጌታ ይሁንብኝ " ትያለሽ ። »

ቁጣዋንና ደስታዋን ለይተው እንደሚያውቁት እየገለፁ ነው።

አስተውሉ!

ዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ ክፉ ቃል አልወጣትም፣ ጮሃም ተንጫጭታም በቁጣ አልተናገረችም። ነገር ግን በሳቸው ላይ ቅር ስተሰኝ አጋጣሚ መሃላ የሚያስፈልገው ጉዳይ ሲገጥማት በስማቸው መማልን ታኮርፍና በነቢዩ ኢብራሂም ጌታ ይሁንብኝ ትላለች።

ቁጣዋ ሲለቃት ግን በሙሐመድ ጌታ ይሁንብኝ ስትል ትምላለች።

ይህንንም ባህሪዋን መልእክተኛው አወቁባትና ነገሯትም።

ስለዚህም የትዳር አጋሮቻችንን ስሜት እዚህ ድረስ ለይቶ ለማወቅ የቅርብ ክትትል ማድረግህ እቤትህ ያለውን ችግር ለመረዳት ራስህንም፣ እሷንም ለማረም ይረዳሃል።

የአላህ መልእክተኛ ﷺ ውዷ ባለቤታቸው ዓኢሻ ቢንት አቢ በክርም ሆነች ሌሎች የምእመናን እናቶች (ረዲየላሁ ዐንሁነ አጅመዒን) በሆነ ጉዳይ ቅር መሰኘታቸውንና ኣለመሰኘታቸውን በትኩረት ይከታተላሉ ይረዱታልም።

እኛም አርዓያነታቸውን አምነን እስከተቀበልንና በተግባር ማዋሉም ተገቢ እንደሆነ እስካመንበት ድረስ፤ ለትዳራችን ስኬት ግራ ቀኝ ብለን ሌላ መፍትሄ ከምናፈላልግ ወይም እያቋቋምን ከምናፈርስ ወደ መመርያችን እንመለስ።

ትዳር ሲባል :

~ ቤት መመስረት፣
~ ገብቶ መብላት፣
~ ለብሶ መውጣት፣
~ ደርሶ መተኛትና
ልጅን መውለድ ብቻ አይደለም።

የራሱ የሆነ ለየት ያለ ዓለም ከመሆኑ አንፃር ጣዕሙና ለዛውም እንደየ ባለትዳሮቹ ይፈራረቃል።

በተሰማራህበት መስክ

•> ህዝብን የምትቀርፅ ሸይኽ ብትሆን፣ 
•> ቀን ከሌት የምትገስፅ ዳዒ ብትሆን፣ 
•> ከሆነ አመራር ድርሻ ቢኖርህ፣
•> ታታሪ ነጋዴም ብትሆን፣
•> ባለ ዓላማ ተማሪ ብትሆን፣
•> ተመራማሪም አጥኚ ብትሆን፣
•> ኑሮን ምትታገል ቅጥረኛም ብትሆን… …

እቤትህ የተገነባው በነበልባል ከሆነ በተለያዩ ክስተቶች እርር… ድብን… ቅጥል የምትልበት እድሉ ስለሚሰፋ ሌሎች ዓላማዬ ብለህ የተነሳህለትን ጉዳዮችህን በተግባር ማዋል የማትችል ትሆናለህ።

ለብሰህ ሲያዩህ የተመቸህ ምሰል እንጂ አቅልህ በሆነ ነገር ርቆሃል።

እንደው ፈገግ ስትልና እኩል ስታወራ የተደላደልክ ብትመስልም ዘወር ስትል የምትተነፍሰው እሳት ነው።

በቆምክበት መድረክ ሁሉ የተረበሽክ ስለምትሆን ብዙ ነገርህ ይምታታል።

የዛሬው ስራህን መገምገሚያ፣ ለነገው ፕሮግራምህ መዘጋጃ የሚሆን ሰላማዊ ቤት ስለሌለህ የቆምክለት ጉዳይም ቤትህም ስልችት ይሉሃል።

የራስህንም ሆነ የባለቤትህን ማንነት በጥልቅ ስላልተረዳህ ጥፋትህን መደበቂያ ሰበብ ፈላጊ ትሆናለህ።

ሁሌም ተሰቃየሁ እንጂ አሰቃይቼ ይሆን ብለህ ራስህን አትገመግምም።

በዚህም ሰበብ ወደቤትህ በመጣህ ቁጥር እሷን ማሸነፍያ ቃላቶችን ስታሰላስል አእምሮህን ወጥረህ…… መሆን የሚገባህንና መስራት የነበረብህን በርካታ ነገሮች ትዘላቸዋለህ።

ሰላም የሌለው ትዳር ማለት የበሽታዎች ሁሉ በሽታ ነው። ያውም ታማሚውና አስታማሚው እኩል የተያዙበት በሽታ።

የዚህ ሁሉ አብዛኛው ሰበቡ አንተው ትሆናለህ።

ሰበብ አታፈላልግ ስህተቷን ብቻ አታጉላ! በደልንም ፍራ!

°°°°°°°✅°°°°°°

ጥቂት የማይባሉ እንስቶች ብዙውን ግዜ በንጭንጬ፣ በጩኸት፣ በችኮላና፣ በቁጣ ሃሳባቸውን ይገልፁ ይሆናል።

ብሶታቸውንም በስድብ፣ በእርግማን፣ በወቀሳና በለቅሶ ያሳዩም ይሆናል።

የዚህን ግዜ ከውጭ ለሚመለከት ታዛቢ ሁለት ነገሮችን ያንፀባርቅለታል።

~ ወይ በጣም የተበደለች
~ ወይ ደግሞ አስቸጋሪ ሚስት ነች የሚል ጥርጣሬ ላይ ያደርሰዋል።

እውነታው ግን አንተጋ ግልፅ ነው። ተበዳይነቷም ሆነ አስቸጋሪነቷ እዚህ ደረጃ ሳይደርስ ማከም የምትችልበት ስልጣንና መፍትሄዎች ሁሉ ተሰጥተውሃል።

ከዚያ ያለፈ ነገር ሆኖ መለያየት ቢከሰት እንኳ ቀድመህ የሚጠበቅብህን ከተወጣህ የሚቆጭህ አትሆንም።

ለሷም የእድሏን ላንተም የድርሻህን የሚሰጥ አምላክ እኮ ነው ያለን። የምን በራስም በሰውም ህይወት መቀለድ ነው

قال تعالى: (وَإِن يَتَفَرَّقَا يُغْنِ اللّهُ كُلاًّ مِّن سَعَتِهِ وَكَانَ اللّهُ وَاسِعًا حَكِيمًا) النساء 130

« ቢለያዩም አላህ ሁሉንም በችሮታው ያብቃቃቸዋል። አላህም ችሮታው ሰፊ ጥበበኛ ነው። » አል ኒሳእ 130

ሁሉም ነገር አስተዳደርና መሪ እንዳለው ሁሉ ትዳርም ብቁ መሪና የሰከነ አስተዳዳሪ ይፈልጋል።

በጣም ጥቃቅን ፍሞችን ከባሎች የአያያዝና የማብረድ ጉድለት የተነሳ በእንስቶቹ እጅ ሲነድ ታየዋለህ።

ወንዶች ዘንድ ተወቃሿ ፣ ተተቺዋና ድሮም እናንተ እየተባለ የሚተረተው በሚስቶች ሲሆንም ትሰማለህ።

በዚያው ልክ ሴቶች ዘንድም ጠቅለል ተደርጎ " ወንዶች ስትባሉ እንደው… … " እየተባለ ሲወገዝ ትሰማለህ።

ይኸ ጥቅል ወቀሳ ግን አጥፊዎችን ከመሸሸግ ውጪ ምንም ጥቅም የለውም።

ይልቅ ከምርጫ ጀምሮ ራስህን አበጅተህና አውቀህ ከገባህበት፤ ከዚያም የሚነሱ አለመግባባቶችን በትእግስት መፍታት ከቻልክ ቤትህ የዱንያ ጀነት አርፎበታልና ምቾታችሁ፣ ድሎታችሁና ደስታችሁ ሁሌም የሚረሳ አይሆንም።

እርግጥ ነው አንተም ሰው ነህና ድክመትም ስህተትም አይለይህም። እንዴት ቤትህን በስርኣት ማስተዳደር ያቅተሃልም አይባልም።

ነገር ግን ሃላፊነትህን ለመወጣት ንቁ ተሳትፎ ካደረክ በአላህ ፈቃድ ብዙዎቹን የትዳርህን ቁስሎች ማከም ትችላለህ።

ለዚህ ብቃትህ ወሳኙ ቁልፍ ደግሞ የአጋርህን ግንዛቤ፣ ባህሪ፣ ፍላጎትና ስሜት እንዲሁም አቅም ማወቅ ነው። ከዚያም ተመጣጣኝ ምላሽ መስጠትህ ነው።

የዚያን ግዜ ድክመታችሁ ማሳበቢያ ስለማይኖረው የግድ ራሳችሁን ለማረም ደፋቀና ትላላችሁ።

ያለዚያ እያለቀስክ ወይም እያስለቀስክ በሁለት በደሎች መሃል መኖር ሊከሰትብህ ይችላል።

መከላከል እየቻሉ ራስን ለጉዳት መዳረግም ሆነ፤ ሌሎችን የሚጎዳ ነገር ማድረግ ደግሞ በነቢያችን ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም አንደበት የተኮነነ ጉዳይ ነው።

قال النبي صلى الله عليه وسلم : (لَا ضَرَرَ وَلَا ضِرَارَ) أخرجه أحمد (2865) وابن ماجه (2341) وصححه الألباني في صحيح ابن ماجه

«(በሸሪዓ) ጉዳትም መጎዳዳትም የለም! » አልሀዲስ

قال رسول الله صلى الله عليه وسلم : ( اتقوا الظلم، فإن الظلم ظلمات يوم القيامة ) رواه مسلم

«በደልን ተጠንቀቁ! የትንሳዔው እለት በደል ጨለማዎች ናትና» ሙስሊም ዘግበውታል

አንተም አትበድል! እንዲበድሉህም አትመቻች!

አላህ የተሳካላቸው ባለ ትዳሮች ያድርገን!!

በደል ከማድረስም ፣ ተበዳይ ከመሆንም ይጠብቀን!!

አሚን!!

የትዳር ውስጥ ችግሮችን መፍታት በተመለከተ ከባልም ይሁን ከሚስት ምን ምን አስተዋፅኦ ይጠበቃል 

والله أعلم، وصلى الله على نبينا محمد وعلى آله وصحبه وسلم تسليما كثيرا.

ke 

yetewesede

Thursday, April 2, 2015

አርቴፊሻል ጥፍር ማስተከል እንዴት ይታያል?



አርቴፊሻል ጥፍር ማስተከል እንዴት ይታያል?

ሰው ሰራሽ ጥፍር ለማስተከል ምክኒያት ሊሆን የሚችለው ከሁለት አንዱ ነው!

1) የተነቀለ ጥፍርን ለመተካት ሊሆን ይችላል፤ ይህ እንደ ህክምና ይታያል። ክልክልም አይሆንም። ለዚህም መረጃ የሚሆነን ቲርሚዚይ የዘገቡትና አልባኒም ሰሂህ ያሉት የዓርፈጃህ ኢብኑል አስዓድ ሀዲስ ነው። በጃሂሊያ ዘመን የተቆረጠ አፍንጫውን የተካበት ብር (silver) ስለበሰበሰ በወርቅ እንዲተካው መልእክተኛው እንደፈቀዱለት ተናግሯል። ይህ የሚያሳየው በዚህ መልክ ጉዳት የደረሰበትን አካል መተካት ችግር እንደሌለው ነው።


እዚህ ላይ ልናጤነው የሚገባው፤
ሀ) ጥፍሩ ረጅም መሆን የለበትም
ለ) ውሀ ከስር ወዳለው የሰውነት ክፍል ይደርስ ዘንድ ለውዱእና ለትጥበት በቀላሉ የሚነሳ አይነት መምረጥ ያስፈልጋል። በጣም የሚያስቸግር ከሆነ ግን ችግር አይኖረውም።

2) ለውበት ጥፍርን መተካት፤
ይህ አይፈቀድም! የዚህም ዋነኛ ምክኒያቱ የአላህን አፈጣጠር መቀየር መሆኑ ነው። እንደዚሁ ሌላ ሰዎች ተፈጥሯዊ ጥፍር እንዲመስላቸው ስለሚያደርግ መሸንገል ነው።

አርቲፊሻል ጥፍር ስለማስረከል በሳውዲ ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴ ተጠይቆ እንደመለሰው፤

" لا يجوز استخدام الأظافر قال علماء اللجنة الدائمة : " لا يجوز استخدام الأظافر الصناعية...؛ لما فيها من الضرر على محالها من الجسم ، ولما فيها -أيضا- من الغش والخداع وتغيير خلق الله ، وبالله التوفيق " انتهى من " فتاوى اللجنة الدائمة ( 17/ 133 ) .

«አርቲፊሻል ጥፍር መጠቀም አይቻልም! ምክኒያቱም፤የሚተከልበት የሰውነት አካል ላይ ጉዳት ያደርሳል! ከዚህም ባሻገር ሰዎችን መሸንገልና ማታለል ነው፤ እንደዚሁ የአላህንም ፍጥረት መቀየር ነው።» በሳውዲ ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴ 17/133

ከ www.facebook.com/tenbihat የተወሰደ።

Sunday, March 15, 2015

6ኛ ሓዲስ






الحديث السادس

الحرام والحلال وفضل الإجتناب الشبهات

عَنْ أَبِي عَبْدِ اللَّهِ النُّعْمَانِ بْنِ بَشِيرٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمَا، قَالَ: سَمِعْت رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ: "إنَّ الْحَلَالَ بَيِّنٌ، وَإِنَّ الْحَرَامَ بَيِّنٌ، وَبَيْنَهُمَا أُمُورٌ مُشْتَبِهَاتٌ لَا يَعْلَمُهُنَّ كَثِيرٌ مِنْ النَّاسِ، فَمَنْ اتَّقَى الشُّبُهَاتِ فَقْد اسْتَبْرَأَ لِدِينِهِ وَعِرْضِهِ، وَمَنْ وَقَعَ فِي الشُّبُهَاتِ وَقَعَ فِي الْحَرَامِ، كَالرَّاعِي يَرْعَى حَوْلَ الْحِمَى يُوشِكُ أَنْ يَرْتَعَ فِيهِ، أَلَا وَإِنَّ لِكُلِّ مَلِكٍ حِمًى، أَلَّا وَإِنَّ حِمَى اللَّهِ مَحَارِمُهُ، أَلَّا وَإِنَّ فِي الْجَسَدِ مُضْغَةً إذَا صَلَحَتْ صَلَحَ الْجَسَدُ كُلُّهُ، وَإذَا فَسَدَتْ فَسَدَ الْجَسَدُ كُلُّهُ، أَلَا وَهِيَ الْقَلْبُ".
رَوَاهُ الْبُخَارِيُّ [رقم:52]، وَمُسْلِمٌ [رقم:1599].


6ኛ ሓዲስ

የሓዲሱ ትርጉም

ሓላል፣ ሓራም፣ እና ተመሳሳይ ነገሮች

ኑዕማን ኢብኑ በሺር የአላህ መልእክተኛ صلى الله عليه وسلم እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋሎህ አለ። የአላህ መልእክተኛ صلى الله عليه وسلمእንዲህ አሉ። “ ሓላል(የተፈቀደ) ነገር ሁሉ ግልጽ ነው። ሃራምም(የተከለከለም) ነገር ግልጽ ነው። በመካከላቸው ደግሞ ብዙ ሰው የማያውቃቸው ተመሳሳይ ነገሮች አሉ።ከነዚህ ተመሳሳይ ነገሮች ራሱን የጠበቀ በርግጥም ዲኑንና (ሃይማኖቱንና) ክብሩን ነጻ አውጥቷል። በነዚህ ተመሳሳይ ነገሮች ላይ የወደቀ ሓራም (ክልክል)ላይ በርግጥም ወደቀ። ተመሳሳይ ነገሮች ላይ የሚወድቅ ሰው አምሳያው ልክ እንደ ወሰን ላይ የሚጠብቅ፥ እንስሶቹ ወሰን አልፈው የሰው እርሻን ሊበሉ እንደቀረቡበት እረኛ ነው። በርግጥም ሁሉም ንጉስ ወሰን አለው፥ የአላህ ወሰን ደግሞ እርም ያደረጋቸው ነገሮች ናቸው። በርግጥም ሰውነት ውስጥ ቁራጭ ስጋ አለች። እሷ ካማረች(ከተስተካከለች) ሰውነት ሁሉ ያምራል(ይስተካከላል)፥ እሷ ደግሞ ከተበላሸች ሰውነት ሁሉ ይበላሻል። ያች ቁራጭ ስጋም ልብ ናት።”
ሓዲሱን ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።

ከስድስተኛው ሓዲስ የምንወስዳቸው ትምህርቶች

1. ሓላል ሁሉ ግልጽ እንደሆነ፥ ሓራም ሁሉ ግልጽ እንደሆነ። በመካከላቸው ግን ተመሳሳይ ነገሮች እንዳሉ፥ እነዚህን ተመሳሳይ ነገሮች ደግሞ ጥቂት ሰው ብቻ እንደሚያውቃቸው።
2. አንድ ነገር ሓላል ነው ወይስ ሓራም ብለን ከተጠራጠርን መራቅ እንዳለብን።
3. ተመሳሳይ ነገሮች የሚሰራ ወደ ግልጽ ሓራም ለመውደቅ ቅርብ እንደሆነ።
4. በምሳሌኣዊ አነጋገር ማስረዳት እንደሚቻል።
5. ነብዩ መሓመድ(ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሱሓቦችን በደንብ እያብራሩ እንዳስተማሩ።
6. ሰው ጥሩና መጥፎ የሚሆነው ዋናው በልቡ እንደሆነ።
7. የሰው ልጅ ውጩ መበላሸት ውስጡ የመበላሸቱ አመላካች እንደሆነ።


Thursday, February 26, 2015

በሒጃብሽ ላይ ፅናት ይኑርሽ!



www.facebook.com/tenbihat የተወሰደ።

በሒጃብሽ ላይ ፅናት ይኑርሽ!

﴿يَا أَيُّهَا النَّبِيُّ قُل لِّأَزْوَاجِكَ وَبَنَاتِكَ وَنِسَاءِ الْمُؤْمِنِينَ يُدْنِينَ عَلَيْهِنَّ مِن جَلَابِيبِهِنَّ ۚ ذَٰلِكَ أَدْنَىٰ أَن يُعْرَفْنَ فَلَا يُؤْذَيْنَ ۗ وَكَانَ اللَّـهُ غَفُورًا رَّحِيمًا﴾
الأحزاب 59


«አንተ ነቢዩ ሆይ! ለሚስቶቸህ፣ ለሴቶች ልጆችህም፣ ለምእምናን ሚስቶችም ከመከናነቢያዎቻቸው በላያቸው ላይ
እንዲለቁ ንገራቸው፡፡ ይህ (በጨዋነታቸው) እንዲታወቁና 
(በባለጌዎች) እንዳይደፈሩ ለመኾን በጣም የቀረበ ነው፡፡ 
አላህም መሓሪ አዛኝ ነው፡፡» 
አል አህዛብ 59

ጅልባብ ማለት ሰውነትን በሙሉ ከላይ ጀምሮ የሚሸፍን ሰፊ የሆነ የልብስ አይነት ነው። አላህ ነብዩን ለሚስቶቻቸው ለልጆቻቸው እንዲሁም ለምእመናት በሙላ ጅልባቦቻቸውን በላያቸው ላይ በመልቀቅ ፊቶቻቸውንና ደረቶቻቸውን ይሸፍኑ ዘንድ እንዲነግሩ አዟቸዋል።

ሴት ልጅ ፊቷን ባእድ ከሆኑና ሙህርሟ ካልሆኑ ወንዶች የመሸፈን ግዴታ እንዳለባት ከቁርንአንና ከሱና የሆኑ ማስረጃዎች አመላክተዋል። አንዲት ሴት ሰውነቷን ከራሷ ጀምሮ እስከ እግሮቿ ድረስ እንድትሸፍን እንዲሁም በእግሯ ላይ ያደረገችው ጌጥ ድምፅ እንዳያሰማ በእግሯ መሬቱን እንዳትመታ ከታዘዘችና በዚህ መልኩ መሸፈን በሷ ላይ ግድ ከሆነ ፊቷን መሸፈኗ ደግሞ በበለጠ ሁኔታ ግድ እንደሚሆንባት ያስተዋይ አእምሮ ባለቤት አይጠራጠርም።

ይህም የሚሆነው ፊቷን በመክፈቷ ሊከሰት የሚችለው ፊትና ጸጉሯን በመክፈቷ ሊከሰት ከሚችለው ፊትና ወይንም የእግር ጥፍሮቿን በመክፈቷ ሊከሰት ከሚችለው ፊትና እጅግ የከበደ በመሆኑ ነው። የአንድ ሙእሚን ሰው አእምሮ የዚህን ሸሪአዊ ህግ ጥበብና ሚስጥር በሚያስተነትን ጊዜ ሴት ልጅ ጸጉሯን አንገቷን ክንዶቿን ባቷንና እግሮቿን ሸፍና እጆቿንና በውበት የተሞላ ፊቷን ከፍታ ትሄድ ዘንድ መፍቀዱ በፍጹም ከሸሪአዊው ጥበብ ጋር ተቃራኒ መሆኑን ያስተውላል።

በአሁን ዘመን ላይ ያለውን የሰዎችን ፊትን በመሸፈን ላይ ያለውን ቸልተኝነት በአንዳንድ ሙስሊም ሃገሮች ሴት ልጅ ከፊቷ ውጪ ያሉትን እንደ ራስ አንገት ደረትና ክንዶቿን ግልታ በየገበያው ላይ በግድ የለሽነት እንድትሄድ እንዳደረገት ያስተዋለ ሰው ሴት ልጅ ፊቷን እንድትሸፍን ያዘዛትን ሸሪአዊ ጥበብ ቁርጠኛ የሆነ ማወቅን ያውቃል።

አንቺ ሙስሊም ሴት ሆይ! አላህን በመፍራት ያንን ከፊትና የጸዳውንና ዋጅብ የሆነውን ከባለቤትና ሙህሪም ከሚሆኑ ወንዶች በስተቀር መላ ሰውነትን የሚሸፍነውን ሸሪአዊ ሂጃብ ልትለብሺ ይገባል። ሴት ልጅ ፊቷንና አንዳንድ የሰውነት ክፍሎቿን ባእድ ለሆኑ ወንዶች መግለጿን ባስተዋልን ጊዜ ብጣም ብዙ የሆኑ ጥፋቶችም ሰብስቦ ይዞ እናገኛለን።

በዚህ ነገር ውስጥ ጥቅም ሊኖር ይችላል ብንል እንኳን ይህ ጥቅም እጅግ በጣም ትንሽ በመሆኑ ከጥፋቶች ውስጥ ተከልሎ ሊታይ አይችልም።

አንዳንዶች የኒቃብን ሸሪዓዊ ብይን አስመልክቶ፤
"ዋጂብ ነው ወይስ መልበሱ በላጭ የሆነ (አፍደል)? " በሚል ጉንጭ አልፋ ክርክር ሴቶችን በማዋከብ ከኒቃብ ያርቃሉ።

ያንቺ አቋም የሚሆነው፤
☞ ዋጂብ ከሆነ መልበስ ግዴታዬን መወጣት ነው!
☞ ዋጂብ ያልሆነ ትርፍ ስራ ከሆነ ከማንም በላይ ወንጀሌን የሚያስምርና ደረጃዬን ከፍ የሚያደርግ መልካም ስራ ያስፈልገኛል የሚል ይሁን።

አላህ ሆይ!

ትክክለኛውን ኢስላማዊ ሂጃብ በመተግበር ላይ ፅናቱን ለግሰኝ!!

www.facebook.com/tenbihat የተወሰደ።

Sunday, February 8, 2015

የጀናዛ ሰላት አሰጋገድ።



የጀናዛ ሰላት አሰጋገድ

አራት ጊዜ ተክቢራ ይደረጋል፤

☞ ከመጀመሪያ ተክቢራ በመቀጠል አል ፋቲሀ (የመክፈቻው ምዕራፍ) ይነበባል። ከዚህም በተጨማሪ አጠር ያለ የቁርአን ምዕራፍ ወይም አንድ ወይም ሁለት አንቀፅ ቢያነብ ጥሩ ነው። ይህንን በማስመልከት ከአብደላህ ኢብን አባስ የተዘገበ ትክክለኛ ሀዲስ ስላለ ነው።


☞ ከዚያም ለሁለተኛ ጊዜ ተክቢራ ይደረጋል፤
ከተሸሁድ ቀጥሎ እንዳለው በነብዩ ላይ ሰለዋት ያወርዳል። ከዚያም በሶስተኛው ተክቢራ ከተደረገ በኃላ እንዲህ ይላል

(اللهم اغفر لِحينا وميتِنا، وشاهدنا وغائبنا، وصغيرنا وكبيرنا، وذَكَرِنا وأنثانَا، اللهم من أحيَيتَهُ منا فأحيه على الإسلام، ومن توفيته منا فَتَوَفهُ على الإيمان، اللهَم اغفر له، وارحمه، وعافه، واعف عنه، وأكرِم نُزُلَه، وَوَسع مُدخَلَه، واغسله بالماء والثلج وِالبرد، ونقه من الخطايا كما ينقى الثوب الأبيض من الدَنس، وأبدلهُ دارا خيرا من داره، وأهلا خيرا من أهله، وأدخله الجنة، وأعذه من عذاب القبر، وعذاب النار، وافسح له في قبره، ونور له فيه، اللهم لا تَحرمنَا أجره ولا تُضِلنا بعده)

(አላሁመ ኢግፊር ሊሐይና ወመይቲና ወሻሂድና ወጋኢቢና ወሰጊሪና ወከቢሪና ወዘከሪና ወኡንሳና አላሁመ መን አህየይተሁ ሚና ፈአህይሂ አለል ኢስላም ወመን ተወፈይተሁ ሚና ፈተወፈሁ አለል ኢማን አላሁመ ኢግፊር ለሁ ወግሲልሁ ቢልማኢ ወሰልጂ ወልበረዲ ወነቂሂ ሚነል ዙኑቢ ወል ኸጣያ ከማ ዩነቀሰውቡል አብየዲ ሚነደነሲ ወአብዲልሁ ዳረን ኸይረን ሚን ዳሪህ ወአህለን ኸይረን ሚን አህሊህ ወአድኺሉሁል ጀነተ ወአዒዙሁ ሚን ዓዛቢል ቀብሪ ወዓዛቢ ናር ወፍሰህ ለሁ ፊ ቀብሪሂ ወናዊርለሁ ፊህ አላሁመ ላተህሪምና አጅረሁ ወላቱዲለና ባዕደሁ።)

ትርጉሙም: “አላህ ሆይ በህይወት ያሉትንም፣ የሞቱትንም፣ በቅርብ ያለውንም ሩቅ ያለውንም፣ ትልልቆችንም፣ ትንንሾችንም፣ ወንዶችንም ፣ ሴቶችንም ማርልን። አላህ ሆይ ከመካከላችን የምትገለውን በእምነት ላይ እንዲሞት አድርገው። አላህ ሆይ ምህረት አድርግለት፣ እዘንለትም፣ ከእሳት ጠብቀው፣ ይቅርም በለው፣ መስተንግዶውን አሳምርለት፣ መግቢያውንም አስፋለት፣ አጢአቱንም በውሃ፣ በበረዶና በቀዝቃዛ ውሃ እጠብለት፣ ነጭ ልበስ ከቆሻሻ እንደሚፀዳው የእርሱንም ወንጀል አፅዳለት፣ ከቤቱ የተሻለ ቤት ከሚስቱ የተሻለ ሚስት ቀይርለት። ወደ ገነት አስገባው፣ ከቀብር ውስጥ ቅጣትና ከእሳትም ቅጣት ጠብቀው ቀብሩንም አስፋለት፣ አብራለት። አላህ ሆይ ምንዳውን አትንፈገን ከእርሱም በኃላ እጣችንን ጥመት አታድርግብን።”
ማለት ነው።

☞ ከአራተኛው ተክቢራ በኃላ በቀኝ ጐኑ ብቻ “አሰላሙአለይኩም” በማለት ያጠናቅቃል።

ተክቢራ በሚደረግበት ጊዜ እጅን ማንሳት ይወደዳል።
√ ሴት ከሆነች ዱዓው ላይ እንዲህ ይባላል፤
(اللهم اغفر لها . . ) (አላሁመ እግፊርለሃ) 
√ ሁለት ከሆኑ ደግሞ (اللهم اغفر لهما . . . ) (አላሁመ እግፊር ለሁማ) 
√ ከሁለት በላይ ከሆኑ ደግሞ (اللهم اغفر لهم . . ) (አላሁመ እግፊር ለሁም) ይባላል። 
√ ሟቹ ህፃን ከሆነ ለእርሱ ምህረትን በዱዓው ውስጥ ከመለመን ይልቅ እንዲህ ይባላል።

(اللهم اجعله فرطا وذُخْرَا لوالديه، وشفيعاَ مُجَابا، اللهم ثقل به موازينهما، وأعظم به أجورهما، وألحقه بصالح سلف المؤمنين، واجعله في كفالة إبراهيم عليه الصلاة والسلام، وَقِهِ برحمتك عذاب الجحيم)

(አላሁመ ኢጅዓሉሁ ፈረጠን ወዙኽረን ሊዋሊደይሂ ፤ ወሸፊዓን ሙጃበን አሏሁመ ሰቂል ቢሂ መዋዚነሁማ፤ ወአዕዚም ቢሂ ኡጁረሁማ፤ ወአልሂቁሁ ቢሷሊሂ ሰለፊልሙእሚኒን፤ ወጅዓልሁ ፊ ከፋለቲ ኢብራሂመ አለይሂ ወሰላቱ ወሰላም ወቂሂ ቢራህመቲከ አዛበል ጀሂም)

√ ትርጉሙም “አላህ ሆይ በወላጆቹ (በወዲያኛው ህይወት) ቀደሞ ሄዶ የሚያመቻች፣ ለችግር ቀን አለኝታ፣ ተሰሚነት ያለው አማላጅ አድርግላቸው፣ አላህ ሆይ የመልካም ስራቸው ሚዛን ማክበጃና የምንዳቸው ማብዣ አድርገው፣ ከደጋግ ምእመናን ጋርም አስጠጋው ከነብዩ ኢብራሂም u እንክብካቤ ስር አድርገው፣ በችሮታህም ከጀሐነም እሳት ጠብቀው።”

☞ ኢማሙ በሟች ላይ ለመስገድ ሲቆም ወንድ ከሆነ በጭንቅላቱ አቅጣጫ ሴት ከሆነች በሰውነቷ መሀል አቅጣጫ መቆሙ ሱና ይሆናል።

☞ አስክሬኑ ወንድና ሴት ከሆኑ ወንዱ ወደ ኢማሙ በኩል ሴቷ ወደ ቂብላ በኩል ይደረጋሉ ።

ከ www.fb.com/easyfiqh የተወሰደ።