Saturday, June 28, 2014

ከአርበዒን አን-ነወውያህ 6ኛ ሓዲስ : ሓላል፣ ሓራም፣ እና ተመሳሳይ ነገሮች

الحديث السادس
"إن الحلال بين وإن الحرام بين"

عَنْ أَبِي عَبْدِ اللَّهِ النُّعْمَانِ بْنِ بَشِيرٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمَا، قَالَ: سَمِعْت رَسُولَ اللَّهِ r يَقُولُ: "إنَّ الْحَلَالَ بَيِّنٌ، وَإِنَّ الْحَرَامَ بَيِّنٌ، وَبَيْنَهُمَا أُمُورٌ مُشْتَبِهَاتٌ لَا يَعْلَمُهُنَّ كَثِيرٌ مِنْ النَّاسِ، فَمَنْ اتَّقَى الشُّبُهَاتِ فَقْد اسْتَبْرَأَ لِدِينِهِ وَعِرْضِهِ، وَمَنْ وَقَعَ فِي الشُّبُهَاتِ وَقَعَ فِي الْحَرَامِ، كَالرَّاعِي يَرْعَى حَوْلَ الْحِمَى يُوشِكُ أَنْ يَرْتَعَ فِيهِ، أَلَا وَإِنَّ لِكُلِّ مَلِكٍ حِمًى، أَلَّا وَإِنَّ حِمَى اللَّهِ مَحَارِمُهُ، أَلَّا وَإِنَّ فِي الْجَسَدِ مُضْغَةً إذَا صَلَحَتْ صَلَحَ الْجَسَدُ كُلُّهُ، وَإذَا فَسَدَتْ فَسَدَ الْجَسَدُ كُلُّهُ، أَلَا وَهِيَ الْقَلْبُ".
رَوَاهُ الْبُخَارِيُّ [رقم:52]، وَمُسْلِمٌ [رقم:1599].  

6ኛ  ሓዲስ
ሓላል፣ ሓራም፣ እና ተመሳሳይ ነገሮች
ከስድስተኛው ሓዲስ የምንወስዳቸው ትምህርቶች
1.      ሓላል ሁሉ ግልጽ እንደሆነ፥ ሓራም ሁሉ ግልጽ እንደሆነ። በመካከላቸው ግን ተመሳሳይ ነገሮች እንዳሉ፥ እነዚህን ተመሳሳይ ነገሮች ደግሞ ጥቂት ሰው ብቻ እንደሚያውቃቸው።
2.     አንድ ነገር ሓላል ነው ወይስ ሓራም ብለን ከተጠራጠርን መራቅ እንዳለብን።
3.     ተመሳሳይ ነገሮች የሚሰራ ወደ ግልጽ ሓራም ለመውደቅ ቅርብ እንደሆነ።
4.     በምሳሌኣዊ አነጋገር ማስረዳት እንደሚቻል።
5.     ነብዩ መሓመድ(ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሱሓቦችን በደንብ እያብራሩ እንዳስተማሩ።
6.     ሰው ጥሩና መጥፎ የሚሆነው ዋናው በልቡ እንደሆነ።
7.     የሰው ልጅ ውጩ መበላሸት ውስጡ የመበላሸቱ አመላካች እንደሆነ።

Thursday, June 26, 2014

‪ለጾም አጋዥ የሆኑ መጽሀፎች‬




ለጾም አጋዥ የሆኑ መጽሀፎች‬ 

ከታች ከተዘረዘሩት ሊንኮች ዳውንሎድ በማድረግ ተጠቃሚ ይሁኑ 
ወይም http://cl.ly/WE8G 
ወይም http://cl.ly/WDR1

‪#‎ 3 ፆመኛ የሆነ ሰው‬ ሊተገብራቸው የሚገቡ ተመራጭ ተግባራት ፓምፕሌት---http://bit.ly/letsomena 
ወይም http://cl.ly/WEAh 


Saturday, June 21, 2014

የረመዳን ስጦታ




--ረመዳንን እንዴት መቀበል ይኖርብናል ?

----->በዑስታዝ ሁሴን ኢሳ እና

---->በኡስታዝ ሡሌይማን አብደላህ 

ዳውንሎድ በማድረግ ያድምጡ ለወዳጅ ዘመድዎም ያስተላልፉ 

Thursday, June 19, 2014

መንዙማ




ታላቁ የተከበረው ወር ረመዳን ደርሷል 

ሽርክ ያነገቡ መንዙማዎች ብቅ ብቅ እያሉ ነው 

ሁላችንም እንጠንቀቅ !!!

Tuesday, June 17, 2014

ከአርበዒን አን-ነወውያህ 5ኛ ሓዲስ በዲን አዲስ ነገር ማምጣት የተከለከለ እንደሆነ።


الحديث الخامس
" من أحدث في أمرنا هذا ما ليس منه فهو رد"

عَنْ أُمِّ الْمُؤْمِنِينَ أُمِّ عَبْدِ اللَّهِ عَائِشَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهَا، قَالَتْ: قَالَ: رَسُولُ اللَّهِ r "مَنْ أَحْدَثَ فِي أَمْرِنَا هَذَا مَا لَيْسَ مِنْهُ فَهُوَ رَدٌّ". رَوَاهُ الْبُخَارِيُّ [رقم:2697]، وَمُسْلِمٌ [رقم:1718].

وَفِي رِوَايَةٍ لِمُسْلِمٍ:"مَنْ عَمِلَ عَمَلًا لَيْسَ عَلَيْهِ أَمْرُنَا فَهُوَ رَدٌّ" .  

5ኛ  ሓዲስ

በዲን አዲስ ነገር ማምጣት የተከለከለ እንደሆነ።

ከአምስተኛው ሓዲስ የምንወስዳቸው ትምህርቶች

1.      በዲን አዲስ ነገር የተሰራ ሁሉ ተቀባይነት እንደሌለው። ሰውየው ጥሩ ንያ ቢኖረውም።
2.     በዲን የታዘዝነውን ስራ ባልታዘዝነው መልኩ መስራት የተከለከለ እንደሆነ።

Saturday, June 14, 2014

ሰላት






ክፍል አንድ 

1. ትርጉሙ፦
ሰላት የዓረብኛ ቋንቋ ትርጉሙ ድዓእ (ልመና) ማለት ሲሆን
ሸሪዓዊ ትርጉሙ ደግሞ፦ በተክቢራ የሚጀመርና በማሰላመት የሚጠናቀቅ ለየት ያሉ ንግግሮችና ተግባሮች ማለት ነው፡፡”
2. ትሩፋቱ፦
ሰላት ከሁለቱ የምስክር ቃሎች ቀጥሎ ከባዱ የኢስላም ማዕዘን ከመሆኑም በላይ የኢስላም ዋናው
መሰረት ነው፡፡ አላህ ነብዩን ወደ ሰማይ በማሳረገ ከሰባቱ ሰማይ በላይ እያሉ ይህን ሰላት መደንገኑ በሙስሊሞች ህይወት ላይ ሰላት ወሳኝ ነገር መሆኑን ይጠቁማል፡፡ ነብዩም አንዳች ነገር ሲገጥማቸው ቶሎ ወደ ሰላት ይሮጡ ነበር፡፡ ስለ ሰላት ትሩፋት የሚገልፁ ሀዲሶች በጣም ብዙ ቢሆኑም የተወሰነውን ብቻ እነሆ፡-
ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል 
“አምስቱ ሰላቶች ከጁምዓ እስከ ጁምዓ ከረመዳን እስከ ረመዳን ታላላቅ ወንጀሎችን ሲቀር በመካከላቸው ያሉትን ኃጢአቶች የሚያብሱ ናቸው::”(ሙስሊም ዘግበውታል)

በሌላም ሀዲስ እንዲህ ብለዋል
“እስቲ ንገሩኝ በደጃፋችሁ ወንዝ ቢኖርና በቀን አምስት ጊዜ በትታጠቡ እድፍ ሊኖርባችሁ ይችላል? ሰሃቦችም “አይኖርም” ሲሉ “ይህ የአምስቱ ሰላቶች ምሳሌ ነው አላህ በእነሱ ሰበብ ኃጠአቶችን ያበሳል” አሉ:: (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)


ከ  www.facebook.com/easyfiqh የተወሰደ።

Thursday, June 12, 2014

የወላጅ ሀቅ



የወላጅ ሀቅ

አዘጋጅ፡- ኡስታዝ ሁሴን ዒሳ

አጭር ማብራሪያ፡- አላሁ ሱብሀነሁ ወተዓላ እራሱና መልእክተኛው ን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ከመታዘዝ ቡኋላ ያዘዘበት ታላቅ ተግባር የወላጆች ሀቅ ነው:: ይህም ሙሐደራ የወላጆችን ሀቅ እንድንገነዘብ የሚረዳ ምርጥ ትምህርት ነው:: 

وَقَضَىٰ رَبُّكَ أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا إِيَّاهُ وَبِالْوَالِدَيْنِ إِحْسَانًا ۚ إِمَّا يَبْلُغَنَّ عِندَكَ الْكِبَرَ أَحَدُهُمَا أَوْ كِلَاهُمَا فَلَا تَقُل لَّهُمَا أُفٍّ وَلَا تَنْهَرْهُمَا وَقُل لَّهُمَا قَوْلًا كَرِيمًا [١٧:٢٣



"ጌታህም (እንዲህ ሲል) አዘዘ፡- እርሱን እንጂ ሌላን አትገዙ፡፡ በወላጆቻችሁም መልካምን ሥሩ፡፡ በአንተ ዘንድ ኾነው አንዳቸው ወይም ሁለታቸው እርጅናን ቢደርሱ ፎህ አትበላቸው፡፡ አትገላምጣቸውም፡፡ ለእነርሱም መልካምን ቃል ተናገራቸው፡፡
" (17:23)

وَاخْفِضْ لَهُمَا جَنَاحَ الذُّلِّ مِنَ الرَّحْمَةِ وَقُل رَّبِّ ارْحَمْهُمَا كَمَا رَبَّيَانِي صَغِيرًا [١٧:٢٤]

"ለሁለቱም ከእዝነትህ የመዋረድን ክንፍ ዝቅ አድርግላቸው፡፡ «ጌታዬ ሆይ! በሕፃንነቴ (በርኅራኄ) እንዳሳደጉኝ እዘንልላቸውም» በል፡፡"(17:24)
ዲን የምግብ ብፌ አይደለም የተመቸነን ይዘን ያልተመቸንን የምንተውበት “አንዱን ጥሎ አንዱን አንጠልጥሎ” እንዳይሆን ነገሩ የወላጆቻችንን ሀቅ ልንጠብቅ ይገባል:: 
ልብ በልልኝ ይህችን አያህ

أَفَتُؤْمِنُونَ بِبَعْضِ الْكِتَابِ وَتَكْفُرُونَ بِبَعْضٍ [٢:٨٥]

"በመጽሐፉ ከፊል ታምናላችሁን? በከፊሉም ትክዳላችሁን?" (2:85)
ያ ራህማን ከወላጆቻችን ሃቅ ጠብቀን ! 
ዳውንሎድ በማድረግ ያድምጡ ለወዳጅ ዘመድዎም ያስተላልፉ። 
ከነዚህ አማራጮች አንዱን በመጫን ዳውንሎድ ያድርጉ፡-